Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.76K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
#ቱሪዝም_ገበታለሀገር_ገበታለትውልድ‼️

ኢትዮጵያ ከቀዳሚዎቹ አምስት የአፍሪካ የቱሪዝም መዳረሻዎች አንዷ እንደትሆን በቱሪዝም የመሠረተ ልማት ሥራዎች ላይ እየሰራ ይገኛል። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ለጂዲፒ ባለው አስተዋፅዖ፣ በሚፈጥረው የሥራ እድልና በሚያስገኘው የውጭ ምንዛሪ የተነሳ እጅግ አስፈላጊ የእድገት ምሰሶ ነው።

ታህሳስ 7 ቀን 2017 ዓም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@ethiopianpressagency...
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍74😁2
#አዲስ_ዘመን_ዛሬ‼️
የታህሳስ 8 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ ዘመን ጋዜጣ
https://press.et/?p=143135
1
ቻይና አረንጓዴ ኢኮኖሚያዊ እድገት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት በንቃት እየተሳተፈች ነው
*****
(ኢ ፕ ድ)

ቻይና በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ቀጣይነት ያለው የአረንጓዴ ልማት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት በንቃት እየተሳተፈችና ድጋፍ እያደረገች መሆኑን በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቸን ሃይ ገለጹ።

አምባሳደሩ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት፤ ቻይና እኤአ በ2030 የካርቦን ልቀትን ለመቀነስና በ2060 ካርቦን ነፃ የሆነ ኢኮኖሚ ለመገንባት የተለያዩ ስትራቴጂዎችንና ፖሊሲዎችን ቀርጻ በመተግበር ላይ ትገኛለች። በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ደረጃ ቀጣይነት ያለው አረንጓዴ ኢኮኖሚያዊ እድገት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥም በንቃት እየተሳተፈችና ድጋፍ እያደረገች ነው ብለዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተነደፈው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርም በፕሬዚዳንት ዢ ጂንፒንግ ይፋ ከተደረገው ሥርዓተ ምሕዳርን የጠበቀ እድገት ማ ስመዝገብ ጋር የሚጣጣም መሆኑንም ጠቁመዋል።

ሁለቱ ሀገራት ቃላቸውን ወደ ተግባር በመቀየር ላይ የሚገኙና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት ምሳሌ የሚሆን ሥራ እየሠሩ ነው ያሉት አምባሳደር ቸን፤ የቻይና ባለሀብቶች የአረንጓዴ ዐሻራ....https://press.et/?p=143140
👍3
ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ግንኙነት ማጠናከር ትሻለች
******
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ግንኙነት ማጠናከር እንደምትሻ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) አስታወቁ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ በጀመረው የኢትዮጵያና የአውሮፓ ኅብረት የስትራቴጂክ አጋርነት መድረክ ላይ ነው።

በመድረኩ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የሚመራ የኢትዮጵያ ልዑክ እና በአዲስ አበባ የሚገኙ የአውሮፓ ኅብረት አባል አገራት አምባሳደሮች እና ተወካዮች እየተሳተፉ ናቸው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ የአውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ ቁልፍ የሠላምና የልማት አጋር መሆኑን ገልጸዋል።

አጋርነቱን ተጠቅማ ኢትዮጵያ ከኅብረቱ ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር እንደምትሻ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ከአውሮፖ ኅብረት አምባሳደሮችና ተወካዮች ጋር የሚደረገው ውይይትም በሠላምና ጸጥታ፣ በኢኮኖሚ ልማትና በባለብዙ ወገን ትብብር ላይ ያተኮረ መሆኑን አመልክተዋል።

በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ለቀጣናው ሠላምና መረጋጋት ወሳኝ ሚና እንዳላት አስረድተዋል።

የአውሮፓ ኅብረት በቀጣናው ሠላምና ደህንነት እንዲሰፍን የበኩልን ድርሻ እንዳለውም መናገራቸውን ውይይቱን የተከታተሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ገልጸዋል።

ኢትዮጵያና የአውሮፓ ኅብረት ያላቸውን ትስስር ለማጠናከር እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ2016 የስትራቴጂክ አጋርነት ትብብር መፈራረማቸው ይታወቃል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ታህሳስ 8 ቀን 2017 ዓም
👍5😁1
ኢትዮጵያ ከ400 በላይ የባቡር ምህንድስና ባለሙያዎች ቢኖሯትም በዘርፉ የተሰማራ ድርጅት የለም
******
(ኢ ፕ ድ)

ኢትዮጵያ ከ400 በላይ የባቡር ምህንድስና ባለሙያዎች ቢኖሯትም፣ በባቡር መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ የተሰማራ ተቋም አለመኖሩን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጌቱ ግዛው (ኢ/ር) ለኢፕድ እንደገለጹት፣በኢትዮጵያ ውስጥ የባቡር መንገድ የሚገነባ አንድም ድርጅት የለም፡፡

በዚህም ኮርፖሬሽኑ በራስ አቅም ወደ ዘርፉ ኮንስትራክሽንና ማማከር ሥራ ለመግባት እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

ወደ ኢንደስትሪው ለመግባት ከፋይናንስ እጥረት ውጪ የባለሙያዎች ችግር እለመኖሩን በመግለጽ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ከ400 በላይ በባቡር ምህንድስና የሰለጠኑ ባለሙያዎች መኖራውን ተናግረዋል።

ኮርፖሬሽኑ ባለሙያዎቹን በመጠቀም በባቡር መንገድ ግንባታ ዘርፍ ለመስራት ማቀዱን ጠቁመው የባለሙያዎች አቅም በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በምስራቅ አፍሪካም ጭምር መስራት የሚስችል ነው በማለት ገልጸዋል፡፡

የፋይናንስ ችግሩን በመቅረፍ እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ ከተለያዩ የውጪ ተባባሪ አካላት ጋር በጋራ እየተሰራ እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡

በማርቆስ በላይ

ታህሳስ 8 ቀን 2017 ዓም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@ethiopianpressagency...
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍7
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 11ኛ መደበኛ ስብሰባው‼️

👉 በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች እንዲሳተፉ የሚፈቅደውን የባንክ ስራ ረቂቅ አዋጅ አፅድቋል፣

👉 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን አፅድቋል ፣

ብሔራዊ ባንክ የውጭ ባንኮችን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር የሚያስችል የአሰራር ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ የምክር ቤት አባላት አሳስበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ፤ የባንክ ሥራ ረቂቅ አዋጅ በፋይናንስ ዘርፉ ዓለም አቀፍ ተወዳደሪ ለመሆንና ኢንቨስትመንትን ለማሳብ ያግዛል።

የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ ይገባሉ ማለት በጋርና በሽርክና ጭምር ከሀገር ውስጥ ባንኮች ጋር በትብብር ይሰራሉ። የባንክ ሥራ ረቂቅ አዋጁ ለሀገር ውስጥ ባንኮችም የዕውቀት ሽግግርን ይፈጥራል።

የሀገር ውስጥ ባንኮችም አቅማቸውን በማጎልበት ተወዳደሪ ለመሆን ሰብሰብ ብለው የፋይናንስ አቅማቸውን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል።

የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የባንክ ስራ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ለምክር ቤቱ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ ቀርቦ መፅደቁን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መረጃ ያመለክታል።

ታህሳስ 8 ቀን 2017 ዓም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@ethiopianpressagency...
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍122👎1
አየር መንገዱ “ኤር ኮንጎ” የሚል ስያሜ የተሰጠው አየር መንገድ አቋቁሞ ስራ አስጀመረ
*****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ጋር በጋራ በመሆን “ኤር ኮንጎ” የሚል ስያሜ የተሰጠው አየር መንገድ አቋቁሞ በይፋ ስራ አስጀመረ።

ኤር ኮንጎ በሁለት ቦይንግ 737 አውሮፕላኖች በሀገሪቱ ውስጥ ባሉ ሰባት ኤርፖርቶች በረራ በማድረግ አገልግሎት መጀመሩን የአየር መንገዱ መረጃ አመላክቷል።

ጥምረቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ራዕይ 2035 አንዱ አካል ሲሆን ከዚህም በፊት በሎሜ አስካይ አየር መንገድ፣ በሊሎንግዌ የማላዊ አየር መንገድ እንዲሁም በሉሳካ የዛምቢያ አየር መንገድን በጋራ ማቋቋሙ ይታወሳል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
👍10
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ.....‼️

✍️ በሁለት ቢሊዮን ብር ወጪ የማሰልጠኛ መሰረተ ልማት ግንባታ ያከናውናል፣

✍️ ከጋቦን የመጡ ከ300 በላይ ሰልጣኞችን ተቀብሎ እያሰለጠነ ይገኛል፣

✍️ በተያዘው በጀት ዓመት ከሁለት ሺህ በላይ ሰልጣኞችን በአቪዬሽን ዘርፍ ለማሰልጠን አቅዷል፣
******
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ ሲቪል #አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመማር ማስተማር አቅሙን ለማሳደግ የተለያዩ የማስልጠኛ መሰረተ ልማቶችን እየገነባ መሆኑን አስታወቀ፡፡ ግንባታው በ12 ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል።

ከጋቦን የመጡ ከ300 በላይ ሰልጣኞችን ተቀብሎ በተለያዩ የአቪዬሽን ሙያዎች እያሰለጠነም ይገኛል።

የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ካሴ ይማም ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ዩኒቨርስቲው ከኢትዮጵያ አልፎ በየዓመቱ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በርካታ ተማሪዎችን በመቀበል አሰልጥኗል።

በተያዘው በጀት ዓመት ከሁለት ሺህ በላይ ሰልጣኞችን በተለያዩ የአቪዬሽን ዘርፍ ለማሰልጠን አቅዶ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በቅርቡ ከተመረቁት ተማሪዎች ከኢትዮጵያና ከ12 #አፍሪካ አገራት የተውጣጡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው በአብራሪነት፣ በአውሮፕላን ቴክኒሺያንነት፣ በበረራ መስተንግዶና በሌሎች የስልጠና መስኮች በዓመት እስከ አራት ሺህ የማሰልጠን አቅም እንዳለው ጠቁመዋል፡፡

በአጠቃላይ ከኢትዮጵያና ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተውጣጡ ከ20 ሺህ በላይ ሰልጣኞችን ማስመረቁ ይታወሳል።

በሄለን ወንድምነው

ታህሳስ 8 ቀን 2017 ዓም
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍62
እንደምን አደሩ‼️
#አዲስ_ዘመን_ዛሬ‼️
የታህሳስ 9 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ ዘመን ጋዜጣ
https://press.et/?p=143199
መልካም ቀን!
👍1
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍1
#የሌማት_ትሩፋት

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ2015 ሀገር በቀሉን የሌማት ትሩፋት መርሐግብር ያስጀመሩ ሲሆን የአራት አመታት የሥራ እቅድ የወተትና ወተት ተዋፅዖ፣ ዶሮ፣ የእንቁላል፣ የማርና የአሳ ምርት ብሎም ምርታማነት ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነው።

በትልቅ ደረጃ ከሚመረቱት ባሻገር በአነስተኛ የመኖሪያ ቤት ደረጃ የሚደረጉ እንደ የጓሮ ዶሮ ርባታ፣ አነስተኛ የአሳ ምርት ሥራ እና የንብ ማነብ እንቅስቃሴዎችን የመደገፍ ሥራም ይሰራል። እነዚህ ሥራዎች በምግብ ራስን በመቻልና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በቤት እና በሀገር ደረጃ በማረጋገጥ ረገድ ወሳኝ
ሚና ይጫወታሉ።

#PMOEthiopia
👍31👎1