ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዳውሮ ዞን የተገነባውን የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካን መረቁ
******
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን የተገነባውን የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳስታወቁት በዛሬው ዕለት በዳውሮ ዞን የተገነባውን የኢቲ ማዕድን ልማት አ.ማ የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካ መርቀን ስራ አስጀምረናል ብለዋል።
ፋብሪካው በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የድንጋይ ከሰል ምርት ከማሻሻል ባሻገር ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች የስራ እድል እንደፈጠረም አስገንዝበዋል፡፡
ጥር 16 ቀን 2017 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን የተገነባውን የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳስታወቁት በዛሬው ዕለት በዳውሮ ዞን የተገነባውን የኢቲ ማዕድን ልማት አ.ማ የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካ መርቀን ስራ አስጀምረናል ብለዋል።
ፋብሪካው በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የድንጋይ ከሰል ምርት ከማሻሻል ባሻገር ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች የስራ እድል እንደፈጠረም አስገንዝበዋል፡፡
ጥር 16 ቀን 2017 ዓም
👍15❤1👏1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን በተገነባው ኢቲ ማዕድን ልማት አ.ማ የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካ ያደረጉት ጉብኝት‼️
ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ታከናውናለች
👉 የሦስትዮሽ የኃይል ሽያጭ ሥምምነት ተፈረመ
*****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የታንዛኒያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያና የኬንያ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኩባንያ ሲያካሂዱት የቆዩትን የሦስትዮሽ የኃይል ሽያጭ ድርድር አጠናቀው ከስምምነት ላይ ደረሱ።
ስምምነቱ በኤሌክትሪክ ሽያጭ የህግ፣ የኮሜርሻልና የቴክኒክ ጉዳዮች ላይ መሠረት ያደረገ እንደሆነም ተገልጿል።
ኢትዮጵያ ከታንዛኒያ ጋር የኃይል ሽያጭ፤ ኬንያ ከታንዛንያ ጋር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኪራይ ውል ስምምነት ተፈራርመዋል።
የኃይል ሽያጭ ሥምምነቱ በሀገራቱ ከፍተኛ ኃላፊዎች ፀድቆ ከሚያዝያ 2017 ዓም ጀምሮ ይተገበራል ተብሏል።
በሥምምነቱ መሠረት ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ታከናውናለች።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህግ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ የሦስትዮሽ ሥምምነቱ ከኃይል ሽያጭ ባለፈ ለቀጣናዊ የንግድና ኢኮኖሚ ትስስር ፋይዳው የጎላ ነውም ብለዋል።
የሦስትዮሽ ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በኬንያ በኩል ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ለማከናወን የሚያስችላትን መብት የሚሰጣት መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ ለሦስትዮሽ ድርድሩ ሴኬት ምስጋና አቅርበዋል።
የታንዛኒያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያ የዕቅድ፣ ምርምር እና ኢንቨስትመንት ምክትል ዳይሬክተር ሚስስ ሬንታ ንድጌ ድርድሩ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እንዳስደሰታቸው ገልፀው ተቋማቱ ለተግባራዊነቱ እንዲሰሩ መጠየቃቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መረጃ ያመለክታል።
ጥር 16 ቀን 2017 ዓም
👉 የሦስትዮሽ የኃይል ሽያጭ ሥምምነት ተፈረመ
*****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የታንዛኒያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያና የኬንያ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኩባንያ ሲያካሂዱት የቆዩትን የሦስትዮሽ የኃይል ሽያጭ ድርድር አጠናቀው ከስምምነት ላይ ደረሱ።
ስምምነቱ በኤሌክትሪክ ሽያጭ የህግ፣ የኮሜርሻልና የቴክኒክ ጉዳዮች ላይ መሠረት ያደረገ እንደሆነም ተገልጿል።
ኢትዮጵያ ከታንዛኒያ ጋር የኃይል ሽያጭ፤ ኬንያ ከታንዛንያ ጋር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኪራይ ውል ስምምነት ተፈራርመዋል።
የኃይል ሽያጭ ሥምምነቱ በሀገራቱ ከፍተኛ ኃላፊዎች ፀድቆ ከሚያዝያ 2017 ዓም ጀምሮ ይተገበራል ተብሏል።
በሥምምነቱ መሠረት ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ታከናውናለች።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህግ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ የሦስትዮሽ ሥምምነቱ ከኃይል ሽያጭ ባለፈ ለቀጣናዊ የንግድና ኢኮኖሚ ትስስር ፋይዳው የጎላ ነውም ብለዋል።
የሦስትዮሽ ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በኬንያ በኩል ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ለማከናወን የሚያስችላትን መብት የሚሰጣት መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ ለሦስትዮሽ ድርድሩ ሴኬት ምስጋና አቅርበዋል።
የታንዛኒያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያ የዕቅድ፣ ምርምር እና ኢንቨስትመንት ምክትል ዳይሬክተር ሚስስ ሬንታ ንድጌ ድርድሩ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እንዳስደሰታቸው ገልፀው ተቋማቱ ለተግባራዊነቱ እንዲሰሩ መጠየቃቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መረጃ ያመለክታል።
ጥር 16 ቀን 2017 ዓም
👍12👎3👏1
በታይላንድ በእስር ላይ የነበሩ 38 ኢትዮጵያዊያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
*******
(ኢ ፕ ድ)
በሥራ ቅጥር ሽፋን በሕገ ወጥ ዓለም አቀፍ የሰው አዘዋዋሪዎች ወደ ማይናማር ተወስደው ችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ለመታደግ መንግሥት ጥረቱን መቀጠሉን ገልጿል፡፡
ከሰሞኑ በሕንድ ኒውዴልሂ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሚሲዮንም ወደ ታይላንድ ልዑክ በመላክ በእስር ላይ ይገኙ የነበሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች እንዲለቀቁ ማድረጉ ተገልጿል፡፡
ማይናማር ውስጥ ከነበሩት መካከልም ከስቸጋሪ ሁኔታ አምልጠው ወደ ታይላንድ የሚገቡ ስደኞች ሕጋዊ ሠነድ ባለመያዛቸው ለእስር ተዳርገው ነበር መባሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡
ይህን ተከትሎም ሚስዮኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ባደረገው ጥረት 38 ኢትዮጵያዊን ከእስር ተለቅቀው ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ማድረጉ ተጠቅሷል፡፡
ጥር 16 ቀን 2017 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
በሥራ ቅጥር ሽፋን በሕገ ወጥ ዓለም አቀፍ የሰው አዘዋዋሪዎች ወደ ማይናማር ተወስደው ችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ለመታደግ መንግሥት ጥረቱን መቀጠሉን ገልጿል፡፡
ከሰሞኑ በሕንድ ኒውዴልሂ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሚሲዮንም ወደ ታይላንድ ልዑክ በመላክ በእስር ላይ ይገኙ የነበሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች እንዲለቀቁ ማድረጉ ተገልጿል፡፡
ማይናማር ውስጥ ከነበሩት መካከልም ከስቸጋሪ ሁኔታ አምልጠው ወደ ታይላንድ የሚገቡ ስደኞች ሕጋዊ ሠነድ ባለመያዛቸው ለእስር ተዳርገው ነበር መባሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡
ይህን ተከትሎም ሚስዮኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ባደረገው ጥረት 38 ኢትዮጵያዊን ከእስር ተለቅቀው ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ማድረጉ ተጠቅሷል፡፡
ጥር 16 ቀን 2017 ዓም
👍11👏3🙏2❤1
❤6👎2👏2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"ያየነውን ለማሳየት እንተጋለን"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
**
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብት የታደለች ሀገር ናት፤ ቢሰራባቸው በዓለም እያየን ከምንደነቅባቸው ስፍራዎች በዕጅጉን የላቁ ውበት ያላቸው ስፍራዎች በሁሉም የኢትዮጵያ አከባቢዎች መኖራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ።
#ጅማ_አባ_ጅፋር_ቤተመንግስት_ዕድሳት #ገበታለትውልድ
ጥር 17 ቀን 2017 ዓም
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
**
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብት የታደለች ሀገር ናት፤ ቢሰራባቸው በዓለም እያየን ከምንደነቅባቸው ስፍራዎች በዕጅጉን የላቁ ውበት ያላቸው ስፍራዎች በሁሉም የኢትዮጵያ አከባቢዎች መኖራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ።
#ጅማ_አባ_ጅፋር_ቤተመንግስት_ዕድሳት #ገበታለትውልድ
ጥር 17 ቀን 2017 ዓም
👍9👏3
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍4
አትሌት ማርታ የ3000 ሜትር ክብረ ወሰን በመስበር አሸነፈች
***
(ኢ ፕ ድ)
በካዛኪስታን ዋና ከተማ አስታን በተካሄደ የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር አትሌት ማርታ አለማየሁ ክብረ ወሰን በመስበር አሸንፋለች።
አትሌት ጉሚ ሽቶ እና አክሱማዊት አምባዬ ውድድሩን ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን አጠናቅቀዋል፡፡
አትሌት ማርታ ርቀቱን ለመጨረስ 8 ደቂቃ ከ39 ሰኮንድ የወሰደባት ሲሆን ውጤቱም ከ18 ዓመት በታች ባሉ አትሌቶች ፈጣኑ ሰዓት ሆኖ በክብረ ወሰንነት መያዙን የወርልድ አትሌቲክስ መረጃ ያመለክታል።
ጥር 17 ቀን 2017 ዓም
***
(ኢ ፕ ድ)
በካዛኪስታን ዋና ከተማ አስታን በተካሄደ የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር አትሌት ማርታ አለማየሁ ክብረ ወሰን በመስበር አሸንፋለች።
አትሌት ጉሚ ሽቶ እና አክሱማዊት አምባዬ ውድድሩን ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን አጠናቅቀዋል፡፡
አትሌት ማርታ ርቀቱን ለመጨረስ 8 ደቂቃ ከ39 ሰኮንድ የወሰደባት ሲሆን ውጤቱም ከ18 ዓመት በታች ባሉ አትሌቶች ፈጣኑ ሰዓት ሆኖ በክብረ ወሰንነት መያዙን የወርልድ አትሌቲክስ መረጃ ያመለክታል።
ጥር 17 ቀን 2017 ዓም
❤11👍4👏1