Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ታከናውናለች

👉 የሦስትዮሽ የኃይል ሽያጭ ሥምምነት ተፈረመ
*****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ  ኃይል፣ የታንዛኒያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያና የኬንያ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኩባንያ ሲያካሂዱት የቆዩትን የሦስትዮሽ የኃይል ሽያጭ ድርድር አጠናቀው ከስምምነት ላይ ደረሱ።

ስምምነቱ በኤሌክትሪክ ሽያጭ የህግ፣ የኮሜርሻልና የቴክኒክ ጉዳዮች ላይ መሠረት ያደረገ እንደሆነም ተገልጿል።

ኢትዮጵያ ከታንዛኒያ ጋር የኃይል ሽያጭ፤ ኬንያ ከታንዛንያ ጋር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኪራይ ውል ስምምነት ተፈራርመዋል።

የኃይል ሽያጭ ሥምምነቱ በሀገራቱ ከፍተኛ ኃላፊዎች ፀድቆ ከሚያዝያ 2017 ዓም ጀምሮ ይተገበራል ተብሏል።

በሥምምነቱ መሠረት ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ታከናውናለች።

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህግ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ የሦስትዮሽ ሥምምነቱ ከኃይል ሽያጭ ባለፈ ለቀጣናዊ የንግድና ኢኮኖሚ ትስስር ፋይዳው የጎላ ነውም ብለዋል።

የሦስትዮሽ ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በኬንያ በኩል ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ለማከናወን የሚያስችላትን መብት የሚሰጣት መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ ለሦስትዮሽ ድርድሩ ሴኬት ምስጋና አቅርበዋል።

የታንዛኒያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያ የዕቅድ፣ ምርምር እና ኢንቨስትመንት ምክትል ዳይሬክተር ሚስስ ሬንታ ንድጌ ድርድሩ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እንዳስደሰታቸው ገልፀው ተቋማቱ ለተግባራዊነቱ እንዲሰሩ መጠየቃቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መረጃ ያመለክታል።

ጥር 16 ቀን 2017 ዓም
👍12👎3👏1
በታይላንድ በእስር ላይ የነበሩ 38 ኢትዮጵያዊያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
*******
(ኢ ፕ ድ)
በሥራ ቅጥር ሽፋን በሕገ ወጥ ዓለም አቀፍ የሰው አዘዋዋሪዎች ወደ ማይናማር ተወስደው ችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ለመታደግ መንግሥት ጥረቱን መቀጠሉን ገልጿል፡፡

ከሰሞኑ በሕንድ ኒውዴልሂ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሚሲዮንም ወደ ታይላንድ ልዑክ በመላክ በእስር ላይ ይገኙ የነበሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች እንዲለቀቁ ማድረጉ ተገልጿል፡፡

ማይናማር ውስጥ ከነበሩት መካከልም ከስቸጋሪ ሁኔታ አምልጠው ወደ ታይላንድ የሚገቡ ስደኞች ሕጋዊ ሠነድ  ባለመያዛቸው ለእስር ተዳርገው ነበር መባሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

ይህን ተከትሎም ሚስዮኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ባደረገው ጥረት 38 ኢትዮጵያዊን ከእስር ተለቅቀው ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ማድረጉ ተጠቅሷል፡፡

ጥር 16 ቀን 2017 ዓም
👍11👏3🙏21
የጅማ አባ ጅፋር ቤተ መንግስት እድሳትና በጅማ የገበታ ለትውልድ ፕሮጄክት ጉብኝት

#PMOEthiopia
6👎2👏2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"ያየነውን ለማሳየት እንተጋለን"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
**
(ኢ ፕ ድ)

ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብት የታደለች ሀገር ናት፤ ቢሰራባቸው በዓለም እያየን ከምንደነቅባቸው ስፍራዎች በዕጅጉን የላቁ ውበት ያላቸው ስፍራዎች በሁሉም የኢትዮጵያ አከባቢዎች መኖራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ።

#ጅማ_አባ_ጅፋር_ቤተመንግስት_ዕድሳት #ገበታለትውልድ

ጥር 17 ቀን 2017 ዓም
👍9👏3
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍4
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የአጋሮና የበሻሻ ህዝብ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያደረገው አቀባበል‼️

#PMOEthiopia
👍7🖕4
አትሌት ማርታ የ3000 ሜትር ክብረ ወሰን በመስበር አሸነፈች
***
(ኢ ፕ ድ)

በካዛኪስታን ዋና ከተማ አስታን በተካሄደ የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር አትሌት ማርታ አለማየሁ ክብረ ወሰን በመስበር አሸንፋለች።

አትሌት ጉሚ ሽቶ እና አክሱማዊት አምባዬ ውድድሩን ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን አጠናቅቀዋል፡፡

አትሌት ማርታ ርቀቱን ለመጨረስ 8 ደቂቃ ከ39 ሰኮንድ የወሰደባት ሲሆን ውጤቱም ከ18 ዓመት በታች ባሉ አትሌቶች ፈጣኑ ሰዓት ሆኖ በክብረ ወሰንነት መያዙን የወርልድ አትሌቲክስ መረጃ ያመለክታል።

ጥር 17 ቀን 2017 ዓም
11👍4👏1
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት‼️

ከህጻንነታቸዉ ጀምሮ በኮልፌ የወንዶች ልጆች ማሳደጊያ እና በቀጨኔ የሴቶች ማሳደጊያ ማዕከል ካሳደግናቸው ልጆቻችን መካከል ሰባቱን ለወግ ለማዕረግ አብቅተን የጋብቻ ስነ ስርዓታቸውን ለመፈጸም ያበቃን ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁን። ሙሽሮች እንኳን ደስ ያላችሁ!

እንኳን ፈጣሪ በህይወት ውጣ ውረድ ውስጥ ረድቷችሁ ለዚህ ለተባረከ እና ለተቀደሰ የህይወታችሁ ምዕራፍ ቀን አደረሳችሁ። መልካም ጋብቻ ይሁንላችሁ!

የከተማ አስተዳደራችን ወላጅ ለሌላቸዉ ወላጅ እና ቤተሰብ በመሆን አሳድጎ፣ ለወግ ለማዕረግ እንዲበቁ ከማድረግ በተጨማሪ በቀጣይ የህይወታቸው ምዕራፍ የስራ እድል በመፍጠር ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ዉጤታማ ህይወት እንዲኖራቸው እየተመኘን በዚህ በተቀደሰ ስራ የተሳተፉትን ሁሉ ላመሰግናቸው እወዳለሁ።

በድጋሚ መልካም ጋብቻ፤ ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ።

ጥር 18 ቀን 2017 ዓም
👍5👏1
ጂማን ዓለም አቀፍ ከተማ ለማድረግ ልንከተላቸው የሚገቡ ዐሥር አቅጣጫዎች
******
(ኢ ፕ ድ)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጂማን ዓለም አቀፍ ከተማ ለማድረግ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች አስቀመጡ።

በዚህም፤

1. ቡናን በጥራትና በስፋት ማምረት፤ በተለይ የጥሪኝ ቡና ስፔሻሊቲን ማስፋፋት፣

2. ልዩ ልዩ ኦርጋኒክ የሻይ ቅጠል ዝርያዎችን በልዩ ብራንድ ጂማ ላይ ማቀነባበር፣

3. የተፈጥሮ ማዳበሪያን በማምረትና በመጠቀም፣ ልዩ ልዩ ፍራፍሬዎችን ማምረት፣ ማሸግና መላክ፣

4. የከብት ወተትና ሥጋ፤ እንዲሁም የዶሮ ዕንቁላል እና ሥጋን በጥራትና በብዛት በማምረት አሽጎ መላክ፣

5. ልዩ ልዩ ቅመማ ቅመም ለውጭ ገበያ በሚመጥን መልኩ ማቀነባበር፣ ማሸግና መላክ፣

6. ልዩ ልዩ የእንጨት ሥራዎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ፣ በፋብሪካዎች በጥራት ማምረት፣

7. የሸክላ ፋብሪዎችን በማስፋፋት፤ ለወለል፣ ለግርግዳ እና ለጣራ የሚያገለግሉ የግንባታ ምርቶችን ወደ ውጭ መላክ፣

8. የጂማንና የአካባቢዋን ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ፣ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ጸጋዎችን በማልማትና በማስተሣሠር የቱሪዝም መዳረሻ ማድረግ፣

9. የጂማ ሕዝብ ከጥንት ጀምሮ የሚታወቅበትን ሰላሙን እና እንግዳ ተቀባይነቱን ማጽናት፣

10. ጎጂ ማኅበራዊ ልማዶችን እና ደካማ የሥራ ባህልን ማሻሻል፣

ጥር 2017 ዓም
👍86👏1