Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.76K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ዛሬ ጥር 23 ቀን 2017 ዓም መካሄድ ይጀምራል
*******
(ኢ ፕ ድ)

የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ ከዛሬ ጥር 23 ቀን ጀምሮ እስከ 25 ቀን 2017 ዓም ድረስ 'ከቃል እስከ ባህል' በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

በጉባኤው ለመሳተፍ፤

👉 የሩሲያው ዩናይትድ ራሺያ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ዲ.ኤ ሜዴቭዴቭ፣

👉 የደቡብ አፍሪካው አፍሪካ ናሽናል ኮንግረንስ ፓርቲ የብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ኖጦሉ ኪይቬት፣

👉 የካዛኪስታን አማናት ፓርቲ እና የሀገሪቱ ፓርላማ የታችኛው ምክር ቤት አባል ሳማት ኑር ታተዛ፣

👉 የኩባው ኮሚኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሜቴ አባል ዩዲ ሜርሴዲስ ኸርናንዴዝ

👉 የቱርኬሚስታን ዲሞክራቲክ ፓርቲ መሪ አታ ሰርዳሮቭ እና በሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛዉ ምስራቅና አፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ያዝጉሊ ማምዶቭ በጉባኤ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።

እንግዶቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በጉባዔው ላይ የጎረቤት ሀገራት እና የብሪክስ አባል ሀገራት እህት ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች ይታደማሉ ተብሏል።

የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ ከጥር 23 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

በማርቆስ በላይ

ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
5👍5👏1
ከባህርና ደረቅ ትራንስፖርት አገልግሎት ከ46 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል
*****
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ባለፋት ስድስት ወራት ከባህርና ደረቅ ትራንስፖርት አገልግሎት 46 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ። 9 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብርም ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ገልጻል።

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ዋና ስራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር)፣ በሰጡት ማብራሪያ፤ በባለፉት ስድስት ወራት ከባህርና ደረቅ ትራንስፖርት አገልግሎት 44 ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 46 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል።

በግማሽ አመቱ 6 ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር ትርፍ ለማግኘት ታቅዶ 9 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ተገኝቷል።

ድርጅቱ በባህርና በደረቅ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፤ አገልግሎቱን በዲጅታል የማዘመን ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል። ደርጅቱ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ሰራዎች እየተሰሩ ነው ሲሉ ጠቁመዋል።

በታደሠ ብናልፈው

ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
4
"የአገው ፈረሰኞች #የኢትዮጵያን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት በማስጠበቅ ታላቅ ሚና ነበራቸው። ለዚህም #የዓድዋ ዘመቻ ተሳትፏቸው ጉልሕ ምስክር ነው። ዛሬም የአባቶቻቸውን ፈለግ በመከተል ሰላምንና ጸጥታን በማስከበር ተገቢውን ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ። ዛሬ የሚከበረው በዓል፣ ፈረሰኞቻችንና ፈረሶቻችን የሰላምና የልማት ዘብ መሆናቸውን ለትውልድ የሚመሰክሩበት እንደሚሆን አምናለሁ"

- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
👏1
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍31🥰1
ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሰጠ የሀዘን መግለጫ‼️

✍️ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በደቡብ ሱዳን ዩኒቲ ግዛት በደረሰው የአውሮፕላን መከስከስ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማውን ሀዘን ገልጿል። በአደጋው የሚወዷቸውን በሞት ላጡ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል። ዩኒቲ ግዛት በደረሰው የአውሮፕላን መከስከስ አደጋ የ20 መንገደኞች ሕይወት አልፏል።

✍️ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በህንድ ኩምብ ሜላ ፌስቲቫል ላይ በሰዎች መብዛት ምክንያት በተፈጠረ ግርግር ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማውን ሀዘን ገልጿል። በተፈጠረ ግርግርም 15 ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል።

በመግለጫው የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ከህንድ ህዝብና መንግስት ጎን መሆኑን ገልጾ፤ ለህንድ ህዝብና መንግስት መጽናናትን ተመኝቷል። በህንድ ፕራያጋራጅ በኩምብ ሜላ ፌስቲቫል በተፈጠረ ግርግርም 15 ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል።

ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
👍51
በጌዴኦ ዞን ለዓባይ ግድብ ግንባታ 16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ
******
(ኢ ፕ ድ)
በጌዴኦ ዞን ባለፈው አንድ ወር ውስጥ በንቅናቄ በተሰራ ሥራ ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የዞኑ የሕዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ገለጸ።

በዞኑ ህብረተሰቡ በቦንድ ግዥ በነቂስ በመሳተፍ ዳግም አሻራውን እያኖረ መሆኑም ተመላክቷል።

የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ብርሃኑ ሮቤ ለኢዜአ እንደገለጹት፥የሕዳሴው ግድብ ዋንጫ ወደዞኑ መምጣትን ተከትሎ ባለፈው አንድ ወር ውስጥ የገቢ ማሰባሰብ ሥራ ተከናውኗል።

የ16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ቦንድ ግዥ የተፈጸመ ሲሆን ተጨማሪ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ ቃል ተገብቷል።

በድጋፉ የመንግስት ሠራተኞች፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ተቋማትና ማህበራት መሳተፋቸውን አመልክተዋል።

የዞኑ ህዝብ በቦንድ ግዥ በነቂስ በመሳተፍ ዳግም አሻራውን ማኖሩንም አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል።

የሕዳሴው ግድብ ዋንጫ በዞኑ የነበረውን የአንድ ወር ቆይታ አጠናቆ ለወላይታ ዞን መሰጠቱን ያነሱት አቶ ብርሃኑ፣ በበጀት ዓመቱ ቀጣይ ወራት ለግድቡ የሚሰበሰበውን ገቢ 60 ሚሊዮን ብር ለማድረስ ታቅዷል ብለዋል።

#ዓባይ #የዓባይ_ግድብ #ኢትዮጵያ #ግብፅ

ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
👍4👏1
በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚመጥን አመራር መስጠት ይገባል
- ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ
*******
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚመጥን ትጋትና ቁርጠኝነት የተላበሰ አመራር መስጠት እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።

አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ከኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሹመት ደብዳቤና የሥራ መመሪያ ተቀብለዋል።

ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆኖ መሾም የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ሃላፊነትና አደራ መጎናጸፍ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውንም ገልጸዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የረጅም ዘመን ግንኙነትን የሚያጠናክር ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ማድረግ እንደሚገባም አስረድተዋል።

በተጨማሪም አሜሪካ በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚገኙባት ሀገር በመሆኗ በኢትዮጵያ ልማትና እድገት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ አምባሳደሩ ጠንካራ ስራ ማከናወን እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።

በመሆኑም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም አሜሪካ ትልቅ እሳቤን የሚጠይቅ ዲፕሎማሲ የሚከናወንባት መሆኑን ታሳቢ ያደረገ አመራር እንዲሰጡም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ወዳጅን ማብዛት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ገልጸዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ፣ በቀጣናው ሰላምና ትብብርን ለመፍጠር ጠንካራ ዲፕሎማሲ እና የውጭ ግንኙነት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ለጀመረችው የፖለቲካና ምጣኔ ሀብት ማሻሻያ ውጤታማነት ከአሜሪካ ጋር በትብብር መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ በቀጣይ በሰላም፣ በጸጥታና በዳያስፖራ ጉዳዮች ዙሪያ ያቀደቻቸውን ግቦች ለማሳካት አምባሳደር ብናልፍ ሚናቸው የጎላ መሆኑን አንስተዋል።

አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት አማካኝነት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
👍51👏1
የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተማሪዎች የተሰሩ የስዕል ጉብኝት‼️

#የብልፅግና_ፓርቲ

ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
👍31👏1