በጌዴኦ ዞን ለዓባይ ግድብ ግንባታ 16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ
******
(ኢ ፕ ድ)
በጌዴኦ ዞን ባለፈው አንድ ወር ውስጥ በንቅናቄ በተሰራ ሥራ ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የዞኑ የሕዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ገለጸ።
በዞኑ ህብረተሰቡ በቦንድ ግዥ በነቂስ በመሳተፍ ዳግም አሻራውን እያኖረ መሆኑም ተመላክቷል።
የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ብርሃኑ ሮቤ ለኢዜአ እንደገለጹት፥የሕዳሴው ግድብ ዋንጫ ወደዞኑ መምጣትን ተከትሎ ባለፈው አንድ ወር ውስጥ የገቢ ማሰባሰብ ሥራ ተከናውኗል።
የ16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ቦንድ ግዥ የተፈጸመ ሲሆን ተጨማሪ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ ቃል ተገብቷል።
በድጋፉ የመንግስት ሠራተኞች፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ተቋማትና ማህበራት መሳተፋቸውን አመልክተዋል።
የዞኑ ህዝብ በቦንድ ግዥ በነቂስ በመሳተፍ ዳግም አሻራውን ማኖሩንም አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል።
የሕዳሴው ግድብ ዋንጫ በዞኑ የነበረውን የአንድ ወር ቆይታ አጠናቆ ለወላይታ ዞን መሰጠቱን ያነሱት አቶ ብርሃኑ፣ በበጀት ዓመቱ ቀጣይ ወራት ለግድቡ የሚሰበሰበውን ገቢ 60 ሚሊዮን ብር ለማድረስ ታቅዷል ብለዋል።
#ዓባይ #የዓባይ_ግድብ #ኢትዮጵያ #ግብፅ
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
በጌዴኦ ዞን ባለፈው አንድ ወር ውስጥ በንቅናቄ በተሰራ ሥራ ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የዞኑ የሕዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ገለጸ።
በዞኑ ህብረተሰቡ በቦንድ ግዥ በነቂስ በመሳተፍ ዳግም አሻራውን እያኖረ መሆኑም ተመላክቷል።
የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ብርሃኑ ሮቤ ለኢዜአ እንደገለጹት፥የሕዳሴው ግድብ ዋንጫ ወደዞኑ መምጣትን ተከትሎ ባለፈው አንድ ወር ውስጥ የገቢ ማሰባሰብ ሥራ ተከናውኗል።
የ16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ቦንድ ግዥ የተፈጸመ ሲሆን ተጨማሪ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ ቃል ተገብቷል።
በድጋፉ የመንግስት ሠራተኞች፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ተቋማትና ማህበራት መሳተፋቸውን አመልክተዋል።
የዞኑ ህዝብ በቦንድ ግዥ በነቂስ በመሳተፍ ዳግም አሻራውን ማኖሩንም አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል።
የሕዳሴው ግድብ ዋንጫ በዞኑ የነበረውን የአንድ ወር ቆይታ አጠናቆ ለወላይታ ዞን መሰጠቱን ያነሱት አቶ ብርሃኑ፣ በበጀት ዓመቱ ቀጣይ ወራት ለግድቡ የሚሰበሰበውን ገቢ 60 ሚሊዮን ብር ለማድረስ ታቅዷል ብለዋል።
#ዓባይ #የዓባይ_ግድብ #ኢትዮጵያ #ግብፅ
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
👍4👏1
በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚመጥን አመራር መስጠት ይገባል
- ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ
*******
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚመጥን ትጋትና ቁርጠኝነት የተላበሰ አመራር መስጠት እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።
አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ከኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሹመት ደብዳቤና የሥራ መመሪያ ተቀብለዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆኖ መሾም የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ሃላፊነትና አደራ መጎናጸፍ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የረጅም ዘመን ግንኙነትን የሚያጠናክር ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ማድረግ እንደሚገባም አስረድተዋል።
በተጨማሪም አሜሪካ በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚገኙባት ሀገር በመሆኗ በኢትዮጵያ ልማትና እድገት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ አምባሳደሩ ጠንካራ ስራ ማከናወን እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።
በመሆኑም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም አሜሪካ ትልቅ እሳቤን የሚጠይቅ ዲፕሎማሲ የሚከናወንባት መሆኑን ታሳቢ ያደረገ አመራር እንዲሰጡም አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ወዳጅን ማብዛት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ገልጸዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ፣ በቀጣናው ሰላምና ትብብርን ለመፍጠር ጠንካራ ዲፕሎማሲ እና የውጭ ግንኙነት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ለጀመረችው የፖለቲካና ምጣኔ ሀብት ማሻሻያ ውጤታማነት ከአሜሪካ ጋር በትብብር መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በቀጣይ በሰላም፣ በጸጥታና በዳያስፖራ ጉዳዮች ዙሪያ ያቀደቻቸውን ግቦች ለማሳካት አምባሳደር ብናልፍ ሚናቸው የጎላ መሆኑን አንስተዋል።
አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት አማካኝነት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
- ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ
*******
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚመጥን ትጋትና ቁርጠኝነት የተላበሰ አመራር መስጠት እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።
አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ከኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሹመት ደብዳቤና የሥራ መመሪያ ተቀብለዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆኖ መሾም የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ሃላፊነትና አደራ መጎናጸፍ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የረጅም ዘመን ግንኙነትን የሚያጠናክር ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ማድረግ እንደሚገባም አስረድተዋል።
በተጨማሪም አሜሪካ በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚገኙባት ሀገር በመሆኗ በኢትዮጵያ ልማትና እድገት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ አምባሳደሩ ጠንካራ ስራ ማከናወን እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።
በመሆኑም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም አሜሪካ ትልቅ እሳቤን የሚጠይቅ ዲፕሎማሲ የሚከናወንባት መሆኑን ታሳቢ ያደረገ አመራር እንዲሰጡም አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ወዳጅን ማብዛት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ገልጸዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ፣ በቀጣናው ሰላምና ትብብርን ለመፍጠር ጠንካራ ዲፕሎማሲ እና የውጭ ግንኙነት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ለጀመረችው የፖለቲካና ምጣኔ ሀብት ማሻሻያ ውጤታማነት ከአሜሪካ ጋር በትብብር መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በቀጣይ በሰላም፣ በጸጥታና በዳያስፖራ ጉዳዮች ዙሪያ ያቀደቻቸውን ግቦች ለማሳካት አምባሳደር ብናልፍ ሚናቸው የጎላ መሆኑን አንስተዋል።
አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት አማካኝነት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
👍5❤1👏1
👍3❤1👏1
“ከቃል እስከ ባህል”
የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ ጀምረናል፤ የኢትዮጵያም ብልጽግና ጉዞ አይቀሬ ነው"
- የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ ጀምረናል፤ የኢትዮጵያም ብልጽግና ጉዞ አይቀሬ ነው"
- የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
👍3👏1