በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚመጥን አመራር መስጠት ይገባል
- ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ
*******
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚመጥን ትጋትና ቁርጠኝነት የተላበሰ አመራር መስጠት እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።
አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ከኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሹመት ደብዳቤና የሥራ መመሪያ ተቀብለዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆኖ መሾም የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ሃላፊነትና አደራ መጎናጸፍ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የረጅም ዘመን ግንኙነትን የሚያጠናክር ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ማድረግ እንደሚገባም አስረድተዋል።
በተጨማሪም አሜሪካ በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚገኙባት ሀገር በመሆኗ በኢትዮጵያ ልማትና እድገት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ አምባሳደሩ ጠንካራ ስራ ማከናወን እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።
በመሆኑም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም አሜሪካ ትልቅ እሳቤን የሚጠይቅ ዲፕሎማሲ የሚከናወንባት መሆኑን ታሳቢ ያደረገ አመራር እንዲሰጡም አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ወዳጅን ማብዛት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ገልጸዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ፣ በቀጣናው ሰላምና ትብብርን ለመፍጠር ጠንካራ ዲፕሎማሲ እና የውጭ ግንኙነት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ለጀመረችው የፖለቲካና ምጣኔ ሀብት ማሻሻያ ውጤታማነት ከአሜሪካ ጋር በትብብር መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በቀጣይ በሰላም፣ በጸጥታና በዳያስፖራ ጉዳዮች ዙሪያ ያቀደቻቸውን ግቦች ለማሳካት አምባሳደር ብናልፍ ሚናቸው የጎላ መሆኑን አንስተዋል።
አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት አማካኝነት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
- ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ
*******
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚመጥን ትጋትና ቁርጠኝነት የተላበሰ አመራር መስጠት እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።
አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ከኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሹመት ደብዳቤና የሥራ መመሪያ ተቀብለዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆኖ መሾም የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ሃላፊነትና አደራ መጎናጸፍ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የረጅም ዘመን ግንኙነትን የሚያጠናክር ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ማድረግ እንደሚገባም አስረድተዋል።
በተጨማሪም አሜሪካ በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚገኙባት ሀገር በመሆኗ በኢትዮጵያ ልማትና እድገት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ አምባሳደሩ ጠንካራ ስራ ማከናወን እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።
በመሆኑም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም አሜሪካ ትልቅ እሳቤን የሚጠይቅ ዲፕሎማሲ የሚከናወንባት መሆኑን ታሳቢ ያደረገ አመራር እንዲሰጡም አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ወዳጅን ማብዛት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ገልጸዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ፣ በቀጣናው ሰላምና ትብብርን ለመፍጠር ጠንካራ ዲፕሎማሲ እና የውጭ ግንኙነት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ለጀመረችው የፖለቲካና ምጣኔ ሀብት ማሻሻያ ውጤታማነት ከአሜሪካ ጋር በትብብር መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በቀጣይ በሰላም፣ በጸጥታና በዳያስፖራ ጉዳዮች ዙሪያ ያቀደቻቸውን ግቦች ለማሳካት አምባሳደር ብናልፍ ሚናቸው የጎላ መሆኑን አንስተዋል።
አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት አማካኝነት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
👍5❤1👏1
👍3❤1👏1
“ከቃል እስከ ባህል”
የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ ጀምረናል፤ የኢትዮጵያም ብልጽግና ጉዞ አይቀሬ ነው"
- የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ ጀምረናል፤ የኢትዮጵያም ብልጽግና ጉዞ አይቀሬ ነው"
- የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
👍3👏1
"የደረጃ ሀሳብ የሌለው ፖለቲካ ፓርቲ የፈለገውን ማፍረስ ቢችልም ለውጥን ለመምራት ይቸገራል"
- የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******
(ኢ ፕ ድ)
የአንድ ፓርቲ አስኳሉ ሀሳብ ነው፤ የደረጃ ሀሳብ የሌለው ፖለቲካ ፓርቲ የፈለገውን ማፍረስ ቢችልም ለውጥን ለመምራት ይቸገራል ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ “ከቃል እስከ ባህል” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባዔው መክፈቻ ስስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ብልጽግና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ለመጀመሪያ አገር በቀል የሆነ እሳቤ ነድፎ የመጣ ፓርቲ ነው፡፡
ሀሳብ የለሽ ፖለቲከኞች፣ፓርቲዎች ለአጭር ጊዜ ድል የረጅም ጊዜን መከራን ያመጡብናል ሲሉም ገልጸዋል፡፡
የአንድ ፓርቲ አስኳሉ ሀሳብ ነው፤ የደረጃ ሀሳብ የሌለው ፖለቲካ ፓርቲ የፈለገውን ማፍረስ ቢችልም ለውጥን ለመምራት ይቸገራል ያሉት የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ብልጽግና ሊያፈርስ የሚፈልገው ኋላቀር አስተሳሰቦችና ልምምዶች ኢትዮጵያ ውስጥ አሉ፡፡
ሊያፈርስ የሚያስበውን አልቆ መገንባትንም አስቀድሞ የሚያስብ ነው። ፒያሳን ማፍረስ ሳይሆን ፒያሳን አልቆ መገንባ የብልጽግና መለያው ነው ብለዋል፡፡
ለውጥ መፍጠር ብቻውን ለውጥ ለመምራት የሚያስችል ብቃት እስካልፈጠረ ድረስ የተሟላ የፓርቲ ህልውና አይኖረውም።
በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የፓርቲው ፕሬዚዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንቶችና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ከመላ ሀገራችን የተውጣጡ ጉባኤተኞች ተገኝተዋል።
ከአስራ አምስት ሀገራት እህት ፓርቲዎች የተወከሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።
"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ቀናት የሚካሄደው የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በርካታ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች የሚተላለፍበት ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
በማርቆስ በላይ
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
- የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******
(ኢ ፕ ድ)
የአንድ ፓርቲ አስኳሉ ሀሳብ ነው፤ የደረጃ ሀሳብ የሌለው ፖለቲካ ፓርቲ የፈለገውን ማፍረስ ቢችልም ለውጥን ለመምራት ይቸገራል ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባዔ “ከቃል እስከ ባህል” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባዔው መክፈቻ ስስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ብልጽግና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ለመጀመሪያ አገር በቀል የሆነ እሳቤ ነድፎ የመጣ ፓርቲ ነው፡፡
ሀሳብ የለሽ ፖለቲከኞች፣ፓርቲዎች ለአጭር ጊዜ ድል የረጅም ጊዜን መከራን ያመጡብናል ሲሉም ገልጸዋል፡፡
የአንድ ፓርቲ አስኳሉ ሀሳብ ነው፤ የደረጃ ሀሳብ የሌለው ፖለቲካ ፓርቲ የፈለገውን ማፍረስ ቢችልም ለውጥን ለመምራት ይቸገራል ያሉት የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ብልጽግና ሊያፈርስ የሚፈልገው ኋላቀር አስተሳሰቦችና ልምምዶች ኢትዮጵያ ውስጥ አሉ፡፡
ሊያፈርስ የሚያስበውን አልቆ መገንባትንም አስቀድሞ የሚያስብ ነው። ፒያሳን ማፍረስ ሳይሆን ፒያሳን አልቆ መገንባ የብልጽግና መለያው ነው ብለዋል፡፡
ለውጥ መፍጠር ብቻውን ለውጥ ለመምራት የሚያስችል ብቃት እስካልፈጠረ ድረስ የተሟላ የፓርቲ ህልውና አይኖረውም።
በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የፓርቲው ፕሬዚዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንቶችና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ከመላ ሀገራችን የተውጣጡ ጉባኤተኞች ተገኝተዋል።
ከአስራ አምስት ሀገራት እህት ፓርቲዎች የተወከሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።
"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ቀናት የሚካሄደው የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በርካታ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች የሚተላለፍበት ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
በማርቆስ በላይ
ጥር 23 ቀን 2017 ዓም
❤3👍2👏1