"ክህሎት ስለ ኢትዮጵያ " የተሰኘ የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ ተከፈተ
****
(ኢፕድ)
በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት "ክህሎት ስለኢትዮጵያ" በሚል የተዘጋጀው የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ እና ፓናል ውይይት በሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ተከፈተ።
የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕዩ በአዲስ አበባ የተከፈተ ሲሆን በዚህም ጥንታዊ የክህሎት አጀማመር መሠረቶች፣ በሰመር ካምፕ እና በስታርት አፕ የተሰሩ ሥራዎች፣ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ተማሪዎች የተሰሩ ማሽኖች እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ የተገኙ ውጤቶች ለእይታ ቀርበዋል።
በመክፈቻው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ተሻለ በሬቻ፣ አቶ ዳንኤል ተሬሳ፣ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፀዳለ ተክሉ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
መድረኩ ''ክህሎት ስለኢትዮጵያ'' በሚል ርዕሰ ጉዳይ የሚካሄድ ይሆናል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) በምዕራፍ አንድ ስለኢትዮጵያ መድረኩ በ14 የተለያዩ ከተሞች በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይትና ምክክር ማካሄዱ ይታወሳል።
ሁለተኛው ምዕራፍ ደግሞ በቡታጅራና በሐረር ተካሄዷል። ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው መድረክ የሁለተኛው ምዕራፍ ሶስተኛ ዙር ነው። በድምሩ "ስለኢትዮጵያ" የተሰኘው መድረክ የዛሬውን ጨምሮ ለ17ተኛ ጊዜ ተካሄዷል።
የኢፕድ ስለኢትዮጵያ የፎቶግራፍ አውደ ርዕይና የፓናል ውይይት የሁለተኛ ምዕራፍ የፎቶግራፍ አውደ ርዕዩና የፓናል ውይይቱ በቀጣይም በተለያዩ ከተሞች እንደሚካሄድ ይጠበቃል።
በሳሙኤል ወንደሰን
****
(ኢፕድ)
በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት "ክህሎት ስለኢትዮጵያ" በሚል የተዘጋጀው የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ እና ፓናል ውይይት በሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ተከፈተ።
የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕዩ በአዲስ አበባ የተከፈተ ሲሆን በዚህም ጥንታዊ የክህሎት አጀማመር መሠረቶች፣ በሰመር ካምፕ እና በስታርት አፕ የተሰሩ ሥራዎች፣ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ተማሪዎች የተሰሩ ማሽኖች እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ የተገኙ ውጤቶች ለእይታ ቀርበዋል።
በመክፈቻው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ተሻለ በሬቻ፣ አቶ ዳንኤል ተሬሳ፣ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፀዳለ ተክሉ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
መድረኩ ''ክህሎት ስለኢትዮጵያ'' በሚል ርዕሰ ጉዳይ የሚካሄድ ይሆናል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) በምዕራፍ አንድ ስለኢትዮጵያ መድረኩ በ14 የተለያዩ ከተሞች በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይትና ምክክር ማካሄዱ ይታወሳል።
ሁለተኛው ምዕራፍ ደግሞ በቡታጅራና በሐረር ተካሄዷል። ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው መድረክ የሁለተኛው ምዕራፍ ሶስተኛ ዙር ነው። በድምሩ "ስለኢትዮጵያ" የተሰኘው መድረክ የዛሬውን ጨምሮ ለ17ተኛ ጊዜ ተካሄዷል።
የኢፕድ ስለኢትዮጵያ የፎቶግራፍ አውደ ርዕይና የፓናል ውይይት የሁለተኛ ምዕራፍ የፎቶግራፍ አውደ ርዕዩና የፓናል ውይይቱ በቀጣይም በተለያዩ ከተሞች እንደሚካሄድ ይጠበቃል።
በሳሙኤል ወንደሰን
👍5
"የየካቲት ወር ሀገርን ሳይሆን አስተሳሰብን ድል የነሳንበት ነው"
- ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል
*******
(ኢ ፕ ድ)
የየካቲት ወር ሀገርን ሳይሆን አስተሳሰብን ድል የነሳንበት ነው ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
ሁለተኛው ምዕራፍ ሦስተኛ ዙር ስለኢትዮጵያ መድረክ "ክህሎት ስለኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ይገኛል።
የየካቲት ወር አባቶቻችን በብዙ መስዋዕትነት ከፍለው የሀገርን ሉዓላዊነት ያስጠበቁበት ነው ያሉት ሚኒስትሯ።
ስለኢትዮጵያ መድረክም የኢትዮጵያ ክብር የሚያሳድጉና የሚያጎለብቱ ተጨባጭ እንዲሁም አሻጋሪ ሃሳቦች የሚንሸራሸሩበት ነው ብለዋል።
በተለይ ሀገሪቱ ክህሎትን በእጅጉ የሚያስፈልጓት ጊዜ በመሆኑ የመድረኩ ሚና ከፍተኛ ስለመሆኑንም ነው ወይዘሮ ሙፈሪሃት የገለጹት።
ሁለተኛውን ዙር ሶስተኛ መድረክ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
መጋቢት 1 ቀን 2017ዓ.ም
- ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል
*******
(ኢ ፕ ድ)
የየካቲት ወር ሀገርን ሳይሆን አስተሳሰብን ድል የነሳንበት ነው ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
ሁለተኛው ምዕራፍ ሦስተኛ ዙር ስለኢትዮጵያ መድረክ "ክህሎት ስለኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ይገኛል።
የየካቲት ወር አባቶቻችን በብዙ መስዋዕትነት ከፍለው የሀገርን ሉዓላዊነት ያስጠበቁበት ነው ያሉት ሚኒስትሯ።
ስለኢትዮጵያ መድረክም የኢትዮጵያ ክብር የሚያሳድጉና የሚያጎለብቱ ተጨባጭ እንዲሁም አሻጋሪ ሃሳቦች የሚንሸራሸሩበት ነው ብለዋል።
በተለይ ሀገሪቱ ክህሎትን በእጅጉ የሚያስፈልጓት ጊዜ በመሆኑ የመድረኩ ሚና ከፍተኛ ስለመሆኑንም ነው ወይዘሮ ሙፈሪሃት የገለጹት።
ሁለተኛውን ዙር ሶስተኛ መድረክ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
መጋቢት 1 ቀን 2017ዓ.ም
👍7❤1
“ትርክት ከሚገነባባቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ ክህሎት ነው”
- ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር)
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ
******
(ኢፕድ)
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ ዶ/ር በክህሎት የበቃ የሰው ሃይል ለአንድ ሀገር ምን አስተዋጽኦ ይኖረዋል በሚል ርዕሰ ጉዳይ ጹሁፍ አቅርበዋል፡፡
ትርክት ከሚገነባባቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ ክህሎት መሆኑን ገልጸው፤ ጥራት ያለው ክህሎት ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ አቅረቦት መር ከሆነው ወደገበያ መር ለመቀየር በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የትራንስፎርሜሽን ጉዟችንን ለማሳካት የክህሎት ሚና ትልቅ ነው ያሉት ዶክተር ተሻለ፤ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ተግባራዊ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ ኢኮኖሚያዊ ስብራትን መጠገን የሚያስችል ክህሎት መር ሥራዎች ተሰርተዋል ነው ያሉት።
ከኢንዱስትሪው እና ከግል ሴክተሩም ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና በባህሪው ተግባር ተኮር መሆኑን አንስተው፤ ተግብር ተኮር ስልጠናን እውን ለማድረግ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ መስራት የሚያስችል ህጋዊ ማዕቀፍ መዘጋጀቱን አብራርተዋል፡፡
እንደ ዶክተር ተሻለ ገለጻ፣ ብቁ የሰው ሃይል ማለት በእውቀት፣ በክህሎት እና በአስተሳሰቡ ዝግጁ የሆነ ነው። የመንግስትና የገል ተቋማት አጋርነታቸውን በማጠናከር እና ክህሎት ልማት ላይ በትኩረት በመስራት በሀገሪቱ ብቁ የሰው ሀይል ማፍራት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል፡፡
የስልጠናን ጥራት ለማምጣት ከኢንዱስትሪዎች ጋር ያለውን ትስስር አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
በቴክኒክና ሙያ ተቋማት በአጫጭር ስልጠና ከሶስት ሚሊዮን በላይ ዜጎች በመደበኛው ደግሞ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎች የሚያልፉ ቢሆንም፤ የክህሎት ልማቱን ከዚህ በላይ ለማሳደግ በትብብር መስራትን ይጠይቃል፡፡
በዘርፉ ያለን ሰዎችም የክህሎት ጥራትን ለማምጣት ያደረግነው ጥረት እና የማስተዋወቅ ስራው በቂ እንዳልሆነ ገልጸው፤ ለክህሎት ልማት ትኩረት መስጠት እና ለሙያና ሙያተኞች የምንሰጠውን ክብርም ማሳደግ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
በሄለን ወንድምነው
መጋቢት 1/2017ዓ.ም
- ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር)
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ
******
(ኢፕድ)
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ ዶ/ር በክህሎት የበቃ የሰው ሃይል ለአንድ ሀገር ምን አስተዋጽኦ ይኖረዋል በሚል ርዕሰ ጉዳይ ጹሁፍ አቅርበዋል፡፡
ትርክት ከሚገነባባቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ ክህሎት መሆኑን ገልጸው፤ ጥራት ያለው ክህሎት ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ አቅረቦት መር ከሆነው ወደገበያ መር ለመቀየር በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የትራንስፎርሜሽን ጉዟችንን ለማሳካት የክህሎት ሚና ትልቅ ነው ያሉት ዶክተር ተሻለ፤ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ተግባራዊ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ ኢኮኖሚያዊ ስብራትን መጠገን የሚያስችል ክህሎት መር ሥራዎች ተሰርተዋል ነው ያሉት።
ከኢንዱስትሪው እና ከግል ሴክተሩም ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና በባህሪው ተግባር ተኮር መሆኑን አንስተው፤ ተግብር ተኮር ስልጠናን እውን ለማድረግ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ መስራት የሚያስችል ህጋዊ ማዕቀፍ መዘጋጀቱን አብራርተዋል፡፡
እንደ ዶክተር ተሻለ ገለጻ፣ ብቁ የሰው ሃይል ማለት በእውቀት፣ በክህሎት እና በአስተሳሰቡ ዝግጁ የሆነ ነው። የመንግስትና የገል ተቋማት አጋርነታቸውን በማጠናከር እና ክህሎት ልማት ላይ በትኩረት በመስራት በሀገሪቱ ብቁ የሰው ሀይል ማፍራት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል፡፡
የስልጠናን ጥራት ለማምጣት ከኢንዱስትሪዎች ጋር ያለውን ትስስር አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
በቴክኒክና ሙያ ተቋማት በአጫጭር ስልጠና ከሶስት ሚሊዮን በላይ ዜጎች በመደበኛው ደግሞ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎች የሚያልፉ ቢሆንም፤ የክህሎት ልማቱን ከዚህ በላይ ለማሳደግ በትብብር መስራትን ይጠይቃል፡፡
በዘርፉ ያለን ሰዎችም የክህሎት ጥራትን ለማምጣት ያደረግነው ጥረት እና የማስተዋወቅ ስራው በቂ እንዳልሆነ ገልጸው፤ ለክህሎት ልማት ትኩረት መስጠት እና ለሙያና ሙያተኞች የምንሰጠውን ክብርም ማሳደግ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
በሄለን ወንድምነው
መጋቢት 1/2017ዓ.ም
👍2❤1
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍5❤1👏1
ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነት ለሙያ እና ሙያተኛ ክብር መስጠት መሆኑን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ገለጹ
- የትርክት መዛባት የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን ጎድቶታትል ብለዋል
****
(ኢፕድ)
ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነት ለሙያ እና ሙያተኛ ክብር መስጠት መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የትርክት መዛባት የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን እንደጎዳውም ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ባደረጉት የማጠቃለያ ንግግር እንደገለጹት፤ ክህሎት በህብረት እና በአንድነት ሆነን ሀገር የምንሰራበት መንገድ ነው፡፡
ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነት ለሙያ እና ሙያተኛ ክብር መስጠት መሆኑን ገልጸው፤ ዜጎች ወርቃማ እጃቸውን ብሩህ አዕምሯቸውን ተጠቅመው የሚያደርጉት የችግር ፈቺነት ተግባር አርበኝነት ነው ብለዋል።
አሁን ያለንበት ወቅት የተዛቡ ትርክቶችን የምንጋፈጥበት ሲሆን፤ ከተዘቡ ትርክቶች አንዱ በሙያ እና ሙያተኞች ያለው ግንዛቤ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የተዘባ ትርክትን ለማስተካከል በኮሚኒኬሽንና በተግባር አሰናስሎ በማስኬድ ተቀራርቦ መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
አይቻልም፣ አይሆንም አትንካ የሚሉት ጉዳዮች የፈጠራን በር የሚዘጉ በመሆናቸው፤ ልጆችን ከልጅነታቸው ጀምሮ ለፈጠራ ያላቸውን ሀሳብ በመደገፍና በማበረታት ማሳደግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ምርታማነት ለማሳደግ እና ዘላቂነት ያለው ኢኮኖሚ ለመገንባት ክህሎት መግቢያ በር መሆኑን አመላክተዋል፡፡
ክህሎት ችግር ፈቺና መፍትሄ አመንጪ ነው ያሉት ሚኒስትሯ፤ እያንዳንዱ አምራች ኢንዱስትሪ የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል ለመገንባት በትብብር መስራት ይገባል ነው ያሉት፡፡
ኢንዱስትሪዎች የሚፈልጓቸው አዳዲስ የስልጠና መስኮች እንዳሉ ገልጸው፤ ትብብርን በማጠናከር ፍላጎት መር የሰው ሃይል ለማቅረብ ይሰራል ብለዋል፡፡
በልምድ እውቀትና ክህሎት ያገኙ ሰዎች እውቅና የሚያገኙበት ስርዓት በተያዘው ዓመት ይፋ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ልንከባከበውና ልንጠብቀው የሚገባ ሀገር በቀል እውቀቶች እንዳሉ ገልጸው፤ 26 የሚደርሱ ሀገር በቀል እውቀቶች ተለይተው ካሪኩለም ተቀርጾላቸዋል ሲሉ አንስተዋል፡፡
በቀጣይም በሀገር በቀል እውቀቶች የማሻሻያ ስራዎች የሚሰራ ሲሆን፤ ይህም ሙያና ሙያተኞችን ለማክበር ጉልህ ሚና አለው ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል አዲስና ነባር ቢዝነሶችን ማጣመር እና ስታርት አፖችን ማጠናከር የግድ እንደሚል ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያን ከፍ ማድረግ የሚቻለው ስራን በክህሎት ሲመራ በመሆኑ ያለንን እውቀት ያለምን ቁጠባ ሀገር ላይ ኢንቨስት እናድረግ ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች ምንም ጥርጥር የለውም ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በሄለን ወንድምነው
- የትርክት መዛባት የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን ጎድቶታትል ብለዋል
****
(ኢፕድ)
ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነት ለሙያ እና ሙያተኛ ክብር መስጠት መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የትርክት መዛባት የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን እንደጎዳውም ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ባደረጉት የማጠቃለያ ንግግር እንደገለጹት፤ ክህሎት በህብረት እና በአንድነት ሆነን ሀገር የምንሰራበት መንገድ ነው፡፡
ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነት ለሙያ እና ሙያተኛ ክብር መስጠት መሆኑን ገልጸው፤ ዜጎች ወርቃማ እጃቸውን ብሩህ አዕምሯቸውን ተጠቅመው የሚያደርጉት የችግር ፈቺነት ተግባር አርበኝነት ነው ብለዋል።
አሁን ያለንበት ወቅት የተዛቡ ትርክቶችን የምንጋፈጥበት ሲሆን፤ ከተዘቡ ትርክቶች አንዱ በሙያ እና ሙያተኞች ያለው ግንዛቤ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የተዘባ ትርክትን ለማስተካከል በኮሚኒኬሽንና በተግባር አሰናስሎ በማስኬድ ተቀራርቦ መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
አይቻልም፣ አይሆንም አትንካ የሚሉት ጉዳዮች የፈጠራን በር የሚዘጉ በመሆናቸው፤ ልጆችን ከልጅነታቸው ጀምሮ ለፈጠራ ያላቸውን ሀሳብ በመደገፍና በማበረታት ማሳደግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ምርታማነት ለማሳደግ እና ዘላቂነት ያለው ኢኮኖሚ ለመገንባት ክህሎት መግቢያ በር መሆኑን አመላክተዋል፡፡
ክህሎት ችግር ፈቺና መፍትሄ አመንጪ ነው ያሉት ሚኒስትሯ፤ እያንዳንዱ አምራች ኢንዱስትሪ የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል ለመገንባት በትብብር መስራት ይገባል ነው ያሉት፡፡
ኢንዱስትሪዎች የሚፈልጓቸው አዳዲስ የስልጠና መስኮች እንዳሉ ገልጸው፤ ትብብርን በማጠናከር ፍላጎት መር የሰው ሃይል ለማቅረብ ይሰራል ብለዋል፡፡
በልምድ እውቀትና ክህሎት ያገኙ ሰዎች እውቅና የሚያገኙበት ስርዓት በተያዘው ዓመት ይፋ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ልንከባከበውና ልንጠብቀው የሚገባ ሀገር በቀል እውቀቶች እንዳሉ ገልጸው፤ 26 የሚደርሱ ሀገር በቀል እውቀቶች ተለይተው ካሪኩለም ተቀርጾላቸዋል ሲሉ አንስተዋል፡፡
በቀጣይም በሀገር በቀል እውቀቶች የማሻሻያ ስራዎች የሚሰራ ሲሆን፤ ይህም ሙያና ሙያተኞችን ለማክበር ጉልህ ሚና አለው ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል አዲስና ነባር ቢዝነሶችን ማጣመር እና ስታርት አፖችን ማጠናከር የግድ እንደሚል ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያን ከፍ ማድረግ የሚቻለው ስራን በክህሎት ሲመራ በመሆኑ ያለንን እውቀት ያለምን ቁጠባ ሀገር ላይ ኢንቨስት እናድረግ ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች ምንም ጥርጥር የለውም ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በሄለን ወንድምነው
👍7❤4🤮2
“የባሕር በር ጥያቄ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው”- ዕምሩ ገመቹ (ዶ/ር)
*****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን፤ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካና ዓለም አቀፍ ግኑኙነት መምህር እምሩ ገመቹ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የሌላ ሀገር ወደብ መጠቀም ከድንገተኛ ቀውሶች ጋር በተያያዘ ዋስትና እንደማይኖረውም አስታውቀዋል።
እምሩ ገመቹ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ ሀገሪቱ ያለችበት የቀይ ባሕርና የህንድ ውቂያኖስ አካባቢ ካለው ጂኦፖለቲካል ስትራቴጂክ አኳያ፤ በርካታ ሀገራት አካባቢውን የመቆጣጠር ፍላጎት አላቸው፤ ይህም እንደ ሀገር የደህንነት ስጋት ይዞ ሊመጣ የሚችል ነው።
ሀገሪቱ የባሕር በር ባለቤት ብትሆን ፤ ብሄራዊ ጥቅሟን ከማስጠበቅ በተጓዳኝ የአካባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ የሚኖራት አበርክቶ ከፍ ያለ እንደሚሆን የጠቆሙት መምህሩ፤ በዓለም አቀፍ መድረክ የሚኖራት ተደማጭነትን ይጨምራል።
የኢንቨስትመንት ስበት በመፍጠር ባለሀብቶች በኢትዮጵያ እንዲያለሙ መደላድል ይፈጠራል፤ የተለያዩ ድጋፎችን እንድታገኝ ይረዳል፤ ይህም ብሄራዊ ጥቅሟን ከማስጠበቅ አንጻር አስተዋጽኦ ይኖረዋል። https://press.et/?p=147260
*****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን፤ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካና ዓለም አቀፍ ግኑኙነት መምህር እምሩ ገመቹ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የሌላ ሀገር ወደብ መጠቀም ከድንገተኛ ቀውሶች ጋር በተያያዘ ዋስትና እንደማይኖረውም አስታውቀዋል።
እምሩ ገመቹ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ ሀገሪቱ ያለችበት የቀይ ባሕርና የህንድ ውቂያኖስ አካባቢ ካለው ጂኦፖለቲካል ስትራቴጂክ አኳያ፤ በርካታ ሀገራት አካባቢውን የመቆጣጠር ፍላጎት አላቸው፤ ይህም እንደ ሀገር የደህንነት ስጋት ይዞ ሊመጣ የሚችል ነው።
ሀገሪቱ የባሕር በር ባለቤት ብትሆን ፤ ብሄራዊ ጥቅሟን ከማስጠበቅ በተጓዳኝ የአካባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ የሚኖራት አበርክቶ ከፍ ያለ እንደሚሆን የጠቆሙት መምህሩ፤ በዓለም አቀፍ መድረክ የሚኖራት ተደማጭነትን ይጨምራል።
የኢንቨስትመንት ስበት በመፍጠር ባለሀብቶች በኢትዮጵያ እንዲያለሙ መደላድል ይፈጠራል፤ የተለያዩ ድጋፎችን እንድታገኝ ይረዳል፤ ይህም ብሄራዊ ጥቅሟን ከማስጠበቅ አንጻር አስተዋጽኦ ይኖረዋል። https://press.et/?p=147260
👎2👏2
"ዛሬ በምሥራቅ ሐረርጌ ቆላማ አካባቢዎች እየለማ የሚገኝ የበጋ ስንዴ ልማትን ተመልክተናል። መትጋት፥መሥራት፥ ማየት ከቻልን፣ ኢትዮጵያ ከመረዳት አልፋ ሌሎችን መርዳት ትችላለች። ይህንን ስራ አጠናክረን እንድንቀጥል አደራ እላለሁ"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
👏2👍1