በአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር በትግራይ ክልል እየተካሄደ ነው
*******************
በትግራይ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ፣ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በአፅቢ ወምበርታ ወረዳ በይፋ ተጀምሯል።
በትግራይ ክልል በአንድ ጀምበር ሶስት ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ነው መርሃ ግበሩ በይፋ የተጀመረው።
በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር እንደትግራይ ክልል በ64 የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች 10 ሚሊዮን ችግኞች መዘጋጀታቸውንም የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል።
ዛሬ በክልሉ በአንድ ጀምበር 3 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተለያዩ የችግኝ አይነቶች የተዘጋጁ ሲሆን በ45 ወረዳዎች 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን የህብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ።
በአስማረ ብርሃኑ
*******************
በትግራይ ክልል የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ፣ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ፣ የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በአፅቢ ወምበርታ ወረዳ በይፋ ተጀምሯል።
በትግራይ ክልል በአንድ ጀምበር ሶስት ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ነው መርሃ ግበሩ በይፋ የተጀመረው።
በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር እንደትግራይ ክልል በ64 የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች 10 ሚሊዮን ችግኞች መዘጋጀታቸውንም የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል።
ዛሬ በክልሉ በአንድ ጀምበር 3 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተለያዩ የችግኝ አይነቶች የተዘጋጁ ሲሆን በ45 ወረዳዎች 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን የህብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ።
በአስማረ ብርሃኑ
👍54❤19👎12👏2
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዕለቱ ለሁለተኛ ጊዜ ባደረጉት ችግኝ ተከላ በየካ ተራራ ከሚገኙ የአንደኛ ደረጃ እና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ጋር በመሆን የ500 ሚልዮን በአንድ ቀን የአረንጓዴ ዐሻራ ተከላ ላይ ተሳትፈዋል።
👍76❤32👎29👏6
የውጭ ሀገራት መገናኛ ብዙኃን በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሐ-ግብርን ሽፋን ሰጥተው እየዘገቡ ይገኛሉ
********************
የቱርኩ ቲ.አር.ቲ-አፍሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ከፍተኛ የችግኝ መትከል ዘመቻ ማካሄድ መጀመራቸውን በፊት ገጹ ይዞ ወጥቷል።
ኢትዮጵያ በቀን 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሐ-ግብር ላይ እያካሄደ እንዳለ ይህም በቀን ውስጥ በርካታ ችግኞችን በመትከል የዓለምን ሪከርድ የሚሰብር መሆኑን ነው የሚዲያው አውታሩ የዘገበው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዲሁም ባለቤታቸው ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው መርሐ-ግብሩን ዛሬ ማለዳ የአፕል ችግኝ በመትከል እንዳስጀመሩትም ቲ.አር.ቲ አስነብቧል።
የቻይናው ሲጂቲኤን-አፍሪካ በበኩሉ፣ 500 ሚሊዮን ችግኞችን በ12 ሰዓታት ውስጥ ለመትከል የሚያስችል ታላቅ መርሐ-ግብር መጀመሩን ገልጾ፣ ይህ ከተሳካ፣ የምሥራቅ አፍሪካን የደን ሽፋን ለማሻሻል ለታቀደው ዕቅድ ትልቅ ብሔራዊ አሻራ ይሆናል ሲል ዘግቧል።
********************
የቱርኩ ቲ.አር.ቲ-አፍሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ከፍተኛ የችግኝ መትከል ዘመቻ ማካሄድ መጀመራቸውን በፊት ገጹ ይዞ ወጥቷል።
ኢትዮጵያ በቀን 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሐ-ግብር ላይ እያካሄደ እንዳለ ይህም በቀን ውስጥ በርካታ ችግኞችን በመትከል የዓለምን ሪከርድ የሚሰብር መሆኑን ነው የሚዲያው አውታሩ የዘገበው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዲሁም ባለቤታቸው ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው መርሐ-ግብሩን ዛሬ ማለዳ የአፕል ችግኝ በመትከል እንዳስጀመሩትም ቲ.አር.ቲ አስነብቧል።
የቻይናው ሲጂቲኤን-አፍሪካ በበኩሉ፣ 500 ሚሊዮን ችግኞችን በ12 ሰዓታት ውስጥ ለመትከል የሚያስችል ታላቅ መርሐ-ግብር መጀመሩን ገልጾ፣ ይህ ከተሳካ፣ የምሥራቅ አፍሪካን የደን ሽፋን ለማሻሻል ለታቀደው ዕቅድ ትልቅ ብሔራዊ አሻራ ይሆናል ሲል ዘግቧል።
👍151❤43👎28👏5
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተካፋይ የነበሩ የትግራይ እግርኳስ ክለቦችን ከመክሰም ለመታደግ ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ሊካሄድ ነው
*********************
በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው መቀለ 70 እንደርታ፣ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲና ስሁል ሽረ ከኢዋይ ፕሮዳክሽን ጋር በመሆን ለ60 ቀን የሚቆይ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር ማዘጋጀታቸውን ይፋ አድርገዋል።
ክለቦቹን ለመደገፍ በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ፕሮግራሞች ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገልጿል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብሩ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል አመራሮች በሚገኙበት መክፈቻውን አዲስ አበባ መዝጊያውን መቀሌ በማድረግ ይካሄዳል ተብሏል።
በፉአድ እድሪስ
*********************
በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው መቀለ 70 እንደርታ፣ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲና ስሁል ሽረ ከኢዋይ ፕሮዳክሽን ጋር በመሆን ለ60 ቀን የሚቆይ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር ማዘጋጀታቸውን ይፋ አድርገዋል።
ክለቦቹን ለመደገፍ በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ፕሮግራሞች ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገልጿል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብሩ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል አመራሮች በሚገኙበት መክፈቻውን አዲስ አበባ መዝጊያውን መቀሌ በማድረግ ይካሄዳል ተብሏል።
በፉአድ እድሪስ
👍34👏24❤11👎10