ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዕለቱ ለሁለተኛ ጊዜ ባደረጉት ችግኝ ተከላ በየካ ተራራ ከሚገኙ የአንደኛ ደረጃ እና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ጋር በመሆን የ500 ሚልዮን በአንድ ቀን የአረንጓዴ ዐሻራ ተከላ ላይ ተሳትፈዋል።
👍76❤32👎29👏6
የውጭ ሀገራት መገናኛ ብዙኃን በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሐ-ግብርን ሽፋን ሰጥተው እየዘገቡ ይገኛሉ
********************
የቱርኩ ቲ.አር.ቲ-አፍሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ከፍተኛ የችግኝ መትከል ዘመቻ ማካሄድ መጀመራቸውን በፊት ገጹ ይዞ ወጥቷል።
ኢትዮጵያ በቀን 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሐ-ግብር ላይ እያካሄደ እንዳለ ይህም በቀን ውስጥ በርካታ ችግኞችን በመትከል የዓለምን ሪከርድ የሚሰብር መሆኑን ነው የሚዲያው አውታሩ የዘገበው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዲሁም ባለቤታቸው ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው መርሐ-ግብሩን ዛሬ ማለዳ የአፕል ችግኝ በመትከል እንዳስጀመሩትም ቲ.አር.ቲ አስነብቧል።
የቻይናው ሲጂቲኤን-አፍሪካ በበኩሉ፣ 500 ሚሊዮን ችግኞችን በ12 ሰዓታት ውስጥ ለመትከል የሚያስችል ታላቅ መርሐ-ግብር መጀመሩን ገልጾ፣ ይህ ከተሳካ፣ የምሥራቅ አፍሪካን የደን ሽፋን ለማሻሻል ለታቀደው ዕቅድ ትልቅ ብሔራዊ አሻራ ይሆናል ሲል ዘግቧል።
********************
የቱርኩ ቲ.አር.ቲ-አፍሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ከፍተኛ የችግኝ መትከል ዘመቻ ማካሄድ መጀመራቸውን በፊት ገጹ ይዞ ወጥቷል።
ኢትዮጵያ በቀን 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሐ-ግብር ላይ እያካሄደ እንዳለ ይህም በቀን ውስጥ በርካታ ችግኞችን በመትከል የዓለምን ሪከርድ የሚሰብር መሆኑን ነው የሚዲያው አውታሩ የዘገበው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዲሁም ባለቤታቸው ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው መርሐ-ግብሩን ዛሬ ማለዳ የአፕል ችግኝ በመትከል እንዳስጀመሩትም ቲ.አር.ቲ አስነብቧል።
የቻይናው ሲጂቲኤን-አፍሪካ በበኩሉ፣ 500 ሚሊዮን ችግኞችን በ12 ሰዓታት ውስጥ ለመትከል የሚያስችል ታላቅ መርሐ-ግብር መጀመሩን ገልጾ፣ ይህ ከተሳካ፣ የምሥራቅ አፍሪካን የደን ሽፋን ለማሻሻል ለታቀደው ዕቅድ ትልቅ ብሔራዊ አሻራ ይሆናል ሲል ዘግቧል።
👍151❤43👎28👏5
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተካፋይ የነበሩ የትግራይ እግርኳስ ክለቦችን ከመክሰም ለመታደግ ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ሊካሄድ ነው
*********************
በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው መቀለ 70 እንደርታ፣ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲና ስሁል ሽረ ከኢዋይ ፕሮዳክሽን ጋር በመሆን ለ60 ቀን የሚቆይ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር ማዘጋጀታቸውን ይፋ አድርገዋል።
ክለቦቹን ለመደገፍ በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ፕሮግራሞች ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገልጿል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብሩ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል አመራሮች በሚገኙበት መክፈቻውን አዲስ አበባ መዝጊያውን መቀሌ በማድረግ ይካሄዳል ተብሏል።
በፉአድ እድሪስ
*********************
በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው መቀለ 70 እንደርታ፣ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲና ስሁል ሽረ ከኢዋይ ፕሮዳክሽን ጋር በመሆን ለ60 ቀን የሚቆይ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር ማዘጋጀታቸውን ይፋ አድርገዋል።
ክለቦቹን ለመደገፍ በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ፕሮግራሞች ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገልጿል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብሩ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል አመራሮች በሚገኙበት መክፈቻውን አዲስ አበባ መዝጊያውን መቀሌ በማድረግ ይካሄዳል ተብሏል።
በፉአድ እድሪስ
👍34👏24❤11👎10
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 75.8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ
*****************************
ኢትዮ ቴሌኮም የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀሙን በተመለከተ ለሚዲያዎች መግለጫ እየሰጠ ነው።
ተቋሙ በ2015 በጀት ዓመት 75.8 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገልፀዋል።
ተቋሙ 18.7 ቢሊየን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱም ተነስቷል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0E4zmQq9ju1SRKgH7YzFiB8ggcg15PKpErhccggqJCvk3ReeModN1tmmSHZKmxeCvl
*****************************
ኢትዮ ቴሌኮም የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀሙን በተመለከተ ለሚዲያዎች መግለጫ እየሰጠ ነው።
ተቋሙ በ2015 በጀት ዓመት 75.8 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገልፀዋል።
ተቋሙ 18.7 ቢሊየን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱም ተነስቷል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0E4zmQq9ju1SRKgH7YzFiB8ggcg15PKpErhccggqJCvk3ReeModN1tmmSHZKmxeCvl
👍56👏16👎14❤5
በአውሮፓ የተከሰተው ከፍተኛ የሙቀት መጠን አስጊ ደረጃ ደርሷል
***********************
በተለይ በደቡባዊ አውሮፓ በቀጣይ ሳምንታት የሙቀት መጠኑ 46 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ይደርሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ቢቢሲ ዘግቧል።
የጣሊያኗ ደሴት ሳርዲኒያ እስከ 46 ዲግሪ ሴንቲግሬድ የደረሰ ሲሆን፤ በቀጣይ 10 ቀናት ከፍተኛ ሙቀት ሊከሰት እንደሚችል ማስጠንቀቂያ እየተሰጠ ነው።
ስፔን በተመሳሳይ ተከታታይ የሆነ የሙቀት ማዕበል የገጠማት ሲሆን፤ በተለይ በደቡባዊ የሀገሪቱ አካባቢ የሙቀት መጠኑ 44 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ደርሷል።
በተጨማሪ፥ በስፔኗ ደሴት ላፓልማ እና በግሪክ የሰደድ እሳት ተከስቷል።
በአሜሪካ ካሊፎርኒያ የሙቀት መጠኑ 49 ዲግሪ ሴንቲግሬድ መድረሱም ነው የተገለፀው።
የሙቀት መጠኑ መጨመር በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ እርምጃዎች መወሰድ እንዳለባቸው ጠቋሚ ነው ሲል ዓለም አቀፉ የሚቲዎሮሎጂ ማህበር አሳስቧል።
***********************
በተለይ በደቡባዊ አውሮፓ በቀጣይ ሳምንታት የሙቀት መጠኑ 46 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ይደርሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ቢቢሲ ዘግቧል።
የጣሊያኗ ደሴት ሳርዲኒያ እስከ 46 ዲግሪ ሴንቲግሬድ የደረሰ ሲሆን፤ በቀጣይ 10 ቀናት ከፍተኛ ሙቀት ሊከሰት እንደሚችል ማስጠንቀቂያ እየተሰጠ ነው።
ስፔን በተመሳሳይ ተከታታይ የሆነ የሙቀት ማዕበል የገጠማት ሲሆን፤ በተለይ በደቡባዊ የሀገሪቱ አካባቢ የሙቀት መጠኑ 44 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ደርሷል።
በተጨማሪ፥ በስፔኗ ደሴት ላፓልማ እና በግሪክ የሰደድ እሳት ተከስቷል።
በአሜሪካ ካሊፎርኒያ የሙቀት መጠኑ 49 ዲግሪ ሴንቲግሬድ መድረሱም ነው የተገለፀው።
የሙቀት መጠኑ መጨመር በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ እርምጃዎች መወሰድ እንዳለባቸው ጠቋሚ ነው ሲል ዓለም አቀፉ የሚቲዎሮሎጂ ማህበር አሳስቧል።
👍62👎8👏6❤5
በሀገሪቱ በቂ የሆነ የስኳር መድሀኒት ስርጭት እና መጠባበቂያ አለ - የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት
**********************************************
ከሰሞኑ በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የስኳር ህሙማን መድሀኒት በተለይም “Humulin70/30” የተባለው የመድሃኒት ዓይነት በቀላሉ ለማግኘት መቸገራቸውን ሲገልጹ ተስተውሏል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ኢቢሲ ሳይበር የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ሰለሞን ንጉሴን አነጋግሯል።
አቶ ሰለሞን ተቋሙ በግዢ የሚያቀርባቸው ህይወት አድን እና መሰረታዊ መድሃኒቶች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ከውጭ እንደሚያስገባ ገልጸው፣ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንድ መሰናክሎች የአቅርቦት መቆራረጥን እንደሚፈጥሩ ጠቁመዋል።
ነገር ግን ተቋሙ ዜጎች እድሜ ልክ የሚወስዷቸው መድሃኒቶችን ቅድሚያ በመስጠት የማቅረብ ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ ባለፉት 2 ዓመታት ምንም አይነት የስኳር መድሃኒት አቅርቦት ችግር እንዳልገጠመ ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0t55HjqaAQpiAnZvgZYiv6gazoDWwfeatPQmxnPE5Pk8c263fBxZWNYdzNgcf4V5Fl
**********************************************
ከሰሞኑ በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የስኳር ህሙማን መድሀኒት በተለይም “Humulin70/30” የተባለው የመድሃኒት ዓይነት በቀላሉ ለማግኘት መቸገራቸውን ሲገልጹ ተስተውሏል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ኢቢሲ ሳይበር የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ሰለሞን ንጉሴን አነጋግሯል።
አቶ ሰለሞን ተቋሙ በግዢ የሚያቀርባቸው ህይወት አድን እና መሰረታዊ መድሃኒቶች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ከውጭ እንደሚያስገባ ገልጸው፣ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንድ መሰናክሎች የአቅርቦት መቆራረጥን እንደሚፈጥሩ ጠቁመዋል።
ነገር ግን ተቋሙ ዜጎች እድሜ ልክ የሚወስዷቸው መድሃኒቶችን ቅድሚያ በመስጠት የማቅረብ ስራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ ባለፉት 2 ዓመታት ምንም አይነት የስኳር መድሃኒት አቅርቦት ችግር እንዳልገጠመ ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0t55HjqaAQpiAnZvgZYiv6gazoDWwfeatPQmxnPE5Pk8c263fBxZWNYdzNgcf4V5Fl
👍74👎18❤15
ከ20 በላይ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ነው
***********
በአገሪቱ የሚገኙ ከ20 በላይ ዩኒቨርስቲዎች በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች በማስመረቅ ላይ ይገኛሉ።
በዛሬው ዕለት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ከሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች መካከል አዲስ አበባ፣ ወለጋ፣ ደብረብርሃን፣ አርባምንጭ፣ ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ እና ሰመራ ዩኒቨርስቲዎች ይገኙበታል፡፡
***********
በአገሪቱ የሚገኙ ከ20 በላይ ዩኒቨርስቲዎች በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች በማስመረቅ ላይ ይገኛሉ።
በዛሬው ዕለት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ከሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች መካከል አዲስ አበባ፣ ወለጋ፣ ደብረብርሃን፣ አርባምንጭ፣ ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ እና ሰመራ ዩኒቨርስቲዎች ይገኙበታል፡፡
👍82❤16👎8👏2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎቹን እያስመረቀ ነው
*******************
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ73ኛ ጊዜ ተማሪዎችን እያስመረቀ ሲሆን በዛሬው ዕለት በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን 8 ሺህ 868 ተማሪዎቹን በማስመረቅ ላይ ይገኛል።
በምረቃ መርሃግብሩ ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጨም ሌሎች የስራ ኃላፊዎች እና እንግዶች ተገኝተዋል።
በአጠቃላይ በዛሬው ዕለት ከሚመረቁ ተማሪዎች መካከል 35 በመቶ ሴቶች ናቸው።
ዩኒቨርስቲው በ18 ካምፓሶቹ በ276 የተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን አሰልጥኖ አስመርቋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02A2dbK9sRryJqcR7tzP1r41jFLg16BV8kpfvF26XXgA91PbujcbhSwc7AwqZ6abm9l
*******************
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ73ኛ ጊዜ ተማሪዎችን እያስመረቀ ሲሆን በዛሬው ዕለት በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን 8 ሺህ 868 ተማሪዎቹን በማስመረቅ ላይ ይገኛል።
በምረቃ መርሃግብሩ ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጨም ሌሎች የስራ ኃላፊዎች እና እንግዶች ተገኝተዋል።
በአጠቃላይ በዛሬው ዕለት ከሚመረቁ ተማሪዎች መካከል 35 በመቶ ሴቶች ናቸው።
ዩኒቨርስቲው በ18 ካምፓሶቹ በ276 የተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን አሰልጥኖ አስመርቋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02A2dbK9sRryJqcR7tzP1r41jFLg16BV8kpfvF26XXgA91PbujcbhSwc7AwqZ6abm9l
👍39❤10👎8👏5