የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የመስቀል ደመራ በዓልን በሰላም ለማክበር ከሃይማኖት አባቶች ጋር ውይይት አደረገ
*************
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የመስቀል ደመራ በዓልን በሰላም ለማክበር ከሃይማኖት አባቶች ጋር በዋና መሥሪያ ቤቱ ውይይት አድርጓል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል፥ ኅብረተሰቡ የመስቀል ደመራ በዓልን በሰላም እንዲያከብር፤ ከውጭ ሀገራት የሚመጡ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ ቱሪስቶች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና ሌሎች ታዳሚዎችም በዓሉን በሰላም አክብረው ወደ መጡበት እንዲመለሱ በቂ የሰው ኃይል እና አነፍናፊ ውሾችን በመጠቀም የተጠናከረ ፍተሻ በማካሄድ አካባቢዎቹን የማጥራት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ፖሊስ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመፍጠር ኦሬንቴሽን በመስጠት ወደ ሥራ መግባቱን እና የፖሊስ ሠራዊቱ በፖሊሳዊ ሥነ-ምግባር በጨዋነት ፍተሻውን እንደሚያካሄድ የገለፁት ኮሚሽነር ጀነራል፤ ሕዝቡም ፍተሻው ለጋራ ጥቅም መሆኑን በመገንዘብ ቀና ትብብር እንዲያደርግ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የሃይማኖት አባቶች በበኩላቸው፥ የፀጥታና ደኅንነት አካላት በዓሉ በሰላም እንዲከበር ተግተው መሥራታቸውን አንስተው ለሠሩት የቅድመ ወንጀል መከላከል ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።
የተከለከሉና የተፈቀዱ ነገሮችን በመለየት ለምዕመናን ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ ማከናወናቸውንም ተናግረዋል።
ሁላችንም የየድርሻችንን በመወጣት፤ ችግሮቻችንን በመቀራረብና በሰላማዊ መንገድ በመፍታት፤ ሰላምን አንግሶ ጥላቻን በማስወገድ በዓሉን በሰላም፣ በደስታ እና በፍቅር ማክበር ይጠበቅብናል ሲሉ የሃይማኖት አባቶች መልዕክት ማስተላለፋቸውን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ መረጃ ያመለክታል።
*************
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የመስቀል ደመራ በዓልን በሰላም ለማክበር ከሃይማኖት አባቶች ጋር በዋና መሥሪያ ቤቱ ውይይት አድርጓል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል፥ ኅብረተሰቡ የመስቀል ደመራ በዓልን በሰላም እንዲያከብር፤ ከውጭ ሀገራት የሚመጡ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ ቱሪስቶች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና ሌሎች ታዳሚዎችም በዓሉን በሰላም አክብረው ወደ መጡበት እንዲመለሱ በቂ የሰው ኃይል እና አነፍናፊ ውሾችን በመጠቀም የተጠናከረ ፍተሻ በማካሄድ አካባቢዎቹን የማጥራት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ፖሊስ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመፍጠር ኦሬንቴሽን በመስጠት ወደ ሥራ መግባቱን እና የፖሊስ ሠራዊቱ በፖሊሳዊ ሥነ-ምግባር በጨዋነት ፍተሻውን እንደሚያካሄድ የገለፁት ኮሚሽነር ጀነራል፤ ሕዝቡም ፍተሻው ለጋራ ጥቅም መሆኑን በመገንዘብ ቀና ትብብር እንዲያደርግ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የሃይማኖት አባቶች በበኩላቸው፥ የፀጥታና ደኅንነት አካላት በዓሉ በሰላም እንዲከበር ተግተው መሥራታቸውን አንስተው ለሠሩት የቅድመ ወንጀል መከላከል ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።
የተከለከሉና የተፈቀዱ ነገሮችን በመለየት ለምዕመናን ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ ማከናወናቸውንም ተናግረዋል።
ሁላችንም የየድርሻችንን በመወጣት፤ ችግሮቻችንን በመቀራረብና በሰላማዊ መንገድ በመፍታት፤ ሰላምን አንግሶ ጥላቻን በማስወገድ በዓሉን በሰላም፣ በደስታ እና በፍቅር ማክበር ይጠበቅብናል ሲሉ የሃይማኖት አባቶች መልዕክት ማስተላለፋቸውን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ መረጃ ያመለክታል።
👍22❤3👏3
በ8 የተለያዩ ቋንቋዎች የተከናወነው የመስቀል ደመራ መዝሙር የመጨረሻው ጥናትና ልምምድ
*********
በ2017 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል ከሚቀርቡ ኃይማኖታዊ ሥርዓቶች አንዱ ለበዓሉ የሚስማማ መዝሙር ነው።
ይህ መዝሙር የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ጊዜ ወስደው የሚዘጋጁበት ነው።
የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ማዕከል ለ2017 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል ሲያደርገው የነበረውን የመዝሙር ጥናት ያጠናቀቀውም ዛሬ ነው።
በዛሬው ዕለትም ነገ በሚከናወነው የመስቀል ደመራ የሚቀርብ መዝሙር የመጨረሻ ጥናትና ልምምድ ተከናውኗል።
ዕለቱን የሚያወድሱ እና ሌሎች የምስጋና መዝሙራትን ጨምሮ የማዕከሉ ዘማሪያን ከ80 በላይ መዝሙራትን ሲያጠኑ ቆይተዋል።
የመዝሙር ጥናቱ በ8 የተለያዩ ቋንቋዎች ማለትም በግዕዝ፣ በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ፣ በትግርኛ፣ በወላይትኛ፣ በጉራግኛ እና በክስታንኛ ተከናውኗል።
ማዕከሉ የዘንድሮውን የመስቀል ደመራ በዓል በደመቀ እና ኃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ለማሳለፍ እንደተዘጋጀም ተገልጿል።
በአሰግድ ሲሳይ
*********
በ2017 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል ከሚቀርቡ ኃይማኖታዊ ሥርዓቶች አንዱ ለበዓሉ የሚስማማ መዝሙር ነው።
ይህ መዝሙር የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ጊዜ ወስደው የሚዘጋጁበት ነው።
የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ማዕከል ለ2017 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል ሲያደርገው የነበረውን የመዝሙር ጥናት ያጠናቀቀውም ዛሬ ነው።
በዛሬው ዕለትም ነገ በሚከናወነው የመስቀል ደመራ የሚቀርብ መዝሙር የመጨረሻ ጥናትና ልምምድ ተከናውኗል።
ዕለቱን የሚያወድሱ እና ሌሎች የምስጋና መዝሙራትን ጨምሮ የማዕከሉ ዘማሪያን ከ80 በላይ መዝሙራትን ሲያጠኑ ቆይተዋል።
የመዝሙር ጥናቱ በ8 የተለያዩ ቋንቋዎች ማለትም በግዕዝ፣ በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ፣ በትግርኛ፣ በወላይትኛ፣ በጉራግኛ እና በክስታንኛ ተከናውኗል።
ማዕከሉ የዘንድሮውን የመስቀል ደመራ በዓል በደመቀ እና ኃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ለማሳለፍ እንደተዘጋጀም ተገልጿል።
በአሰግድ ሲሳይ
👍55❤15👎10👏2
Forwarded from FM ADDIS 97.1(ኤፍ ኤም አዲስ 97.1)
ቅኝት ስፖርት ኤፍ ኤም አዲስ 97.1
ማንቸስተር ዩናይትድ ከትዌንቴ የዩሮፓ ሊግ
https://www.facebook.com/share/v/YBKyx6SqqbdSmnv6/?mibextid=oFDknk
ማንቸስተር ዩናይትድ ከትዌንቴ የዩሮፓ ሊግ
https://www.facebook.com/share/v/YBKyx6SqqbdSmnv6/?mibextid=oFDknk
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
👍8❤6
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የምድብ 3ኛ እና 4ኛ ጨዋታዎቹን በኮትዲቯር ያደርጋል
*************
ዋልያዎቹ ከጊኒ ጋር የሚያደርጓቸው እነዚህ የደርሶ መልስ መረሐ ግብሮች በኮትዲቯር እንደሚደረጉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታውቋል።
የሁለቱ ሀገራት የመጀመሪያ ጨዋታ ጊኒ የሜዳዋ ጨዋታዋን ለማድረግ ባስመዘገበችውና በያሞሱክሩ በሚገኘው ስታድ ኮናን ባኒ ስታዲየም ጥቅምት 1/2017 ከምሽቱ 1፡00 ላይ ይከናወናል።
ሁለተኛው ጨዋታ ደግሞ ኢትዮጵያ ባስመዘገበችውና አቢጃን በሚገኘው ስታድ ደ ኢቢምፔ ስታዲየም ጥቅምት 4/2017 ምሸት 4፡00 ላይ ይደረጋል።
ሞሮኮ በ2025 ለምታሰናዳው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ እስካሁን ሁለት ጨዋታዎችን ያደረጉት ዋልያዎቹ አንድ ነጥብ በመያዝ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
ጊኒ በአንጻሩ እስካሁን ምንም ነጥብ አላስመዘገበችም።
በዮሴፍ ሹምዬ
*************
ዋልያዎቹ ከጊኒ ጋር የሚያደርጓቸው እነዚህ የደርሶ መልስ መረሐ ግብሮች በኮትዲቯር እንደሚደረጉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታውቋል።
የሁለቱ ሀገራት የመጀመሪያ ጨዋታ ጊኒ የሜዳዋ ጨዋታዋን ለማድረግ ባስመዘገበችውና በያሞሱክሩ በሚገኘው ስታድ ኮናን ባኒ ስታዲየም ጥቅምት 1/2017 ከምሽቱ 1፡00 ላይ ይከናወናል።
ሁለተኛው ጨዋታ ደግሞ ኢትዮጵያ ባስመዘገበችውና አቢጃን በሚገኘው ስታድ ደ ኢቢምፔ ስታዲየም ጥቅምት 4/2017 ምሸት 4፡00 ላይ ይደረጋል።
ሞሮኮ በ2025 ለምታሰናዳው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ እስካሁን ሁለት ጨዋታዎችን ያደረጉት ዋልያዎቹ አንድ ነጥብ በመያዝ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
ጊኒ በአንጻሩ እስካሁን ምንም ነጥብ አላስመዘገበችም።
በዮሴፍ ሹምዬ
👍31❤3👎3
ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የተ.መ.ድ. ዋና ጸሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሀና ቴቴን አሰናበቱ
**************
ፕሬዚዳንቷ በዚሁ ወቅት ልዩ መልዕክተኛዋ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ቀንድ ላበረከቱት ከፍተኛ ድጋፍ ማመስገናቸውን የፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
**************
ፕሬዚዳንቷ በዚሁ ወቅት ልዩ መልዕክተኛዋ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ቀንድ ላበረከቱት ከፍተኛ ድጋፍ ማመስገናቸውን የፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
👍44❤12
ኢትዮጵያ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን በመከላከል ረገድ ላስመዘገበችዉ አመርቂ ዉጤት እዉቅና አገኘች
********************
በኒውዮርክ እየተካሄደ በሚገኘው የተመድ 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ግብረ ሃይል (ኤንሲዲ) ለኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ሽልማት አበርክቷል።
እውቅናው የተሰጠው ኢትዮጵያ የተቀናጀ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ስራዎችን በማከናወን እና ማህበረሰቡን ያማከለ አገልግሎት መስጠት በመቻሏ በተለይም የማህፀን ጫፍ ካንሰርን በመከላከል ላስመዘገበችው ውጤት መሆኑ ተገልጿል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የጤና ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሽልማቱን መቀበላቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
********************
በኒውዮርክ እየተካሄደ በሚገኘው የተመድ 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ግብረ ሃይል (ኤንሲዲ) ለኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ሽልማት አበርክቷል።
እውቅናው የተሰጠው ኢትዮጵያ የተቀናጀ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ስራዎችን በማከናወን እና ማህበረሰቡን ያማከለ አገልግሎት መስጠት በመቻሏ በተለይም የማህፀን ጫፍ ካንሰርን በመከላከል ላስመዘገበችው ውጤት መሆኑ ተገልጿል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የጤና ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሽልማቱን መቀበላቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
👍29❤2