ርዕሰ መስተዳደር ሽመልስ አብዲሳ በኦሮሚያ ክልል የተጀመረውን አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት የስራ እንቅስቃሴ ጎበኙ
********************
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ ከፍያለው ተፈራ በክልሉ የተጀመረውን አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ጠዴ ድልዲማ በመገኘት ጎብኝተዋል፡፡
በምስራቅ ሸዋ ዞን 302 ቀበሌዎች በአዲሱ አደረጃጀት የተዋቀሩ ሲሆን 281 የሚሆኑት ወደ ስራ መግባታቸዉን የዞኑ አስተዳደር አቶ አባቦ ማሞ ገልፀዋል::
በሉሜ ወረደ የጠዴ ድልዲማ ቀበሌ አስተዳደር ወ/ሮ ትግስት ኢብራህም የህዝብ አገልግሎት በቀበሌ ደረጃ እንዲሰጥ መደረጉ የበለጠ አመራሩ እራሱን ሰጥቶ ህዝቡን በንቃት እንዲገለግል አድርጎታል ብለዋል::
ነዋሪዎችም አገልግሎት በቅርበት ማግኘታቸው እንዳስደታቸው እና ግዜያቸዉን እንደቆጠበላቸዉ ገልፀዋል::
በዓሊ ደደፎ
********************
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ ከፍያለው ተፈራ በክልሉ የተጀመረውን አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ጠዴ ድልዲማ በመገኘት ጎብኝተዋል፡፡
በምስራቅ ሸዋ ዞን 302 ቀበሌዎች በአዲሱ አደረጃጀት የተዋቀሩ ሲሆን 281 የሚሆኑት ወደ ስራ መግባታቸዉን የዞኑ አስተዳደር አቶ አባቦ ማሞ ገልፀዋል::
በሉሜ ወረደ የጠዴ ድልዲማ ቀበሌ አስተዳደር ወ/ሮ ትግስት ኢብራህም የህዝብ አገልግሎት በቀበሌ ደረጃ እንዲሰጥ መደረጉ የበለጠ አመራሩ እራሱን ሰጥቶ ህዝቡን በንቃት እንዲገለግል አድርጎታል ብለዋል::
ነዋሪዎችም አገልግሎት በቅርበት ማግኘታቸው እንዳስደታቸው እና ግዜያቸዉን እንደቆጠበላቸዉ ገልፀዋል::
በዓሊ ደደፎ
👍18👎5
የመስከረም ስጦታው የሙዚቃ ንጉሥ፦ ክቡር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ
********************
ለግማሽ ምዕተ ዓመት በኢትዮጵያ ሙዚቃ ግንባር ቀደም ሆኖ ካለፉት ኮከቦች መካከል አንዱ ነበር፤ ለዚህም ነው "የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ" የሚል መጠሪያ የተሰጠው፡፡
"በፀሐይ ብርሃን ደምቃ፣ ክረምትና በጋ፤
የትውልድ አገር ያላት፣ የአስራ ሦስት ወር ጸጋ፤…" በሚለው እና ከመስከረም ጀምሮ እስከ ቡሄ በሚዘልቀው ዜማው የኢትዮጵያውያንን ውብ የዓውደ ዓመት አከባበር ባህል በአእምሮአችን የሚስልልን ባለዜማን መስከረም ለኢትዮጵያ የለገሰችው እንዲህ እንደሚንቆለጳጵሳት አውቃ ይሆን ያስብላል! ጥላሁን፦
"አቤት በአዲሱ ዓመት - ዘመኑ ሲለወጥ፣
ያበቦቹ ሽታ - መዓዛው ሲመስጥ፤
ኮበሌውም ሲጨፍር - ሲል መስከረም ጠባዬ፤
ኮረዳዋም ባቅሟ - ስትዞር በራሷ ቀዬ፤…" እያለ ነው ኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመትን ለአዲስ ህይወት እና አዲስ ተስፋ ጅማሮ እንደ ንጋት የሚቀበሏትን መስከረም ያወሳት፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡- https://ebc.et/newsdetails.aspx?newsid=7879
********************
ለግማሽ ምዕተ ዓመት በኢትዮጵያ ሙዚቃ ግንባር ቀደም ሆኖ ካለፉት ኮከቦች መካከል አንዱ ነበር፤ ለዚህም ነው "የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ" የሚል መጠሪያ የተሰጠው፡፡
"በፀሐይ ብርሃን ደምቃ፣ ክረምትና በጋ፤
የትውልድ አገር ያላት፣ የአስራ ሦስት ወር ጸጋ፤…" በሚለው እና ከመስከረም ጀምሮ እስከ ቡሄ በሚዘልቀው ዜማው የኢትዮጵያውያንን ውብ የዓውደ ዓመት አከባበር ባህል በአእምሮአችን የሚስልልን ባለዜማን መስከረም ለኢትዮጵያ የለገሰችው እንዲህ እንደሚንቆለጳጵሳት አውቃ ይሆን ያስብላል! ጥላሁን፦
"አቤት በአዲሱ ዓመት - ዘመኑ ሲለወጥ፣
ያበቦቹ ሽታ - መዓዛው ሲመስጥ፤
ኮበሌውም ሲጨፍር - ሲል መስከረም ጠባዬ፤
ኮረዳዋም ባቅሟ - ስትዞር በራሷ ቀዬ፤…" እያለ ነው ኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመትን ለአዲስ ህይወት እና አዲስ ተስፋ ጅማሮ እንደ ንጋት የሚቀበሏትን መስከረም ያወሳት፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡- https://ebc.et/newsdetails.aspx?newsid=7879
👍19❤6
ምስጢረኞቹ ቀጠሮ የማያዛንፉት የመስቀል ስጦታዎች
የመስቀል ወፍ እና አደይ አበባ የት ነው የሚደበቁት?
*******
የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት የብሩህ ተስፋ ተምሳሌት ነው፡፡ ከጨለማ ወደ ብርሃን መውጫ፣ ከአሮጌ ወደ አዲስ መሸጋገሪያ ነው፡፡ መስከረም ላይ በሚጀመረው የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ብዙዎች ተስፋቸው እንደ ብራው ሰማይ ይፈካል፣ ከከርሞ ህልማቸው ጋር ይቀጣጠራሉ፡፡
በአሮጌው ዘመን ያሰለቻቸውን አሮጌ አስተሳሰብ ትተው በአዲስ መንፈስ ለአዲስ ስኬት ይዘጋጃሉ፤ የመስቀሏ ወፍ ላባዋን እንደምትቀይረው ኢትዮጵያውያንም ራሳቸውን አንጽተው ለቀጣዩ ፍሬያማ ጉዞ ይዘጋጃሉ፡፡ ምድር በዐደይ አበባ እንደምታጌጠው ኢትዮጵያውያንም በፀዓዳ ልብሳቸው ያጌጣሉ፡፡
መስከረም እንደ ሀገር የዘመን መቁጠሪያ ሆኖ በአንድነት የሚከበር ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የሚገኙ አብዛኛዎቹ ብሔሮችም እንደ አዲስ ዘመን መባቻቸው አድርገው በተለያዩ ስያሜዎች ያከብሩታል፡፡ ደመራ ደምረው ሕብራቸውን ያደምቁበታል፤ ችቦ አብርተው መጻኢ ብርሃናቸውን ያዩበታል፡፡ ይህ ተፈጥሮን የተከተለ አከባበር በውስጡ በርካታ ምሥጢሮችን የያዘ የኢትዮጵያውያን ብቻ ሀብት ነው፡፡
መስቀል ሲመጣ ቀጠሮአቸውን የማያዛንፉት የመስቀል ወፍ እና ዐደይ አበባ ደግሞ የኢትዮጵያ ተስፋ ብስራት አድማቂዎች ናቸው፡፡
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0ovWdqpuXWcUeyGuFangBugRf8Rn7oJgU8Q9HupVmyrY5w8VK1oGJC6ogHehkKF5bl
የመስቀል ወፍ እና አደይ አበባ የት ነው የሚደበቁት?
*******
የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት የብሩህ ተስፋ ተምሳሌት ነው፡፡ ከጨለማ ወደ ብርሃን መውጫ፣ ከአሮጌ ወደ አዲስ መሸጋገሪያ ነው፡፡ መስከረም ላይ በሚጀመረው የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ብዙዎች ተስፋቸው እንደ ብራው ሰማይ ይፈካል፣ ከከርሞ ህልማቸው ጋር ይቀጣጠራሉ፡፡
በአሮጌው ዘመን ያሰለቻቸውን አሮጌ አስተሳሰብ ትተው በአዲስ መንፈስ ለአዲስ ስኬት ይዘጋጃሉ፤ የመስቀሏ ወፍ ላባዋን እንደምትቀይረው ኢትዮጵያውያንም ራሳቸውን አንጽተው ለቀጣዩ ፍሬያማ ጉዞ ይዘጋጃሉ፡፡ ምድር በዐደይ አበባ እንደምታጌጠው ኢትዮጵያውያንም በፀዓዳ ልብሳቸው ያጌጣሉ፡፡
መስከረም እንደ ሀገር የዘመን መቁጠሪያ ሆኖ በአንድነት የሚከበር ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የሚገኙ አብዛኛዎቹ ብሔሮችም እንደ አዲስ ዘመን መባቻቸው አድርገው በተለያዩ ስያሜዎች ያከብሩታል፡፡ ደመራ ደምረው ሕብራቸውን ያደምቁበታል፤ ችቦ አብርተው መጻኢ ብርሃናቸውን ያዩበታል፡፡ ይህ ተፈጥሮን የተከተለ አከባበር በውስጡ በርካታ ምሥጢሮችን የያዘ የኢትዮጵያውያን ብቻ ሀብት ነው፡፡
መስቀል ሲመጣ ቀጠሮአቸውን የማያዛንፉት የመስቀል ወፍ እና ዐደይ አበባ ደግሞ የኢትዮጵያ ተስፋ ብስራት አድማቂዎች ናቸው፡፡
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0ovWdqpuXWcUeyGuFangBugRf8Rn7oJgU8Q9HupVmyrY5w8VK1oGJC6ogHehkKF5bl
👍17❤10
እንኳን ለመስቀል በዓል በሠላም አደረሳችሁ!! - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
*****************
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፏል፡፡
አገልግሎቱ በዓሉን አስመልክቶ ያስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-
ኢትዮጵያ ካላት ሃይማኖታዊና ባህላዊ በዓላቶቻችን አንዱ የመስቀልና የደመራ በዓል ነው፡፡ በመላዉ ኢትዮጵያ መስከረም 16 የደመራ በዓል ተብሎ እንዲሁም መስከረም 17 ቀን የሚከበረዉ የመስቀል በዓል ጥንታዊነቱን ይዞ የቀጠለ የዐደባባይ በዓል በመሆኑ ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበቻቸዉ ቀርሶቻችን አንዱ ነው፡፡ የዐደባባይ በዓላቶቻችን የአብሮነት እሴቶቻችንን የሚያጎሉ፣ የብዝኃነታችን ጌጥነት ማሳያዎች ከመሆን ባሻገር የበርካታ ጎብኝዎችን ቀልብ የሚስቡ ሀብቶቻችን እየሆኑ መጥተዋል፡፡
መስከረም በርከት ያሉ በዓለት የምናከብርበት ወር ነው፤ ዛሬ እንኳ የመስቀል በዓልን ስናከብር የዓለም የቱሪዝም ቀንን ጭምር እያከበርን ነው፡፡ የዓለም ቱሪዝም ቀን በ1980 (እ.አ.አ) በተባበሩት መንግሥታት የዓለም ቱሪዝም ድርጅት ሐውልት መቆምን ምክንያት ተደርጎ የተመረጠ የቱሪዝም መታሰቢያ ቀን ነው፡፡
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0ZFexyc8JkA9T3VV5XN7gWhvoB3kbuKwYyL3Jgnm5vebfgbcqd6NqKQ5kfKLdDMhKl
*****************
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፏል፡፡
አገልግሎቱ በዓሉን አስመልክቶ ያስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-
ኢትዮጵያ ካላት ሃይማኖታዊና ባህላዊ በዓላቶቻችን አንዱ የመስቀልና የደመራ በዓል ነው፡፡ በመላዉ ኢትዮጵያ መስከረም 16 የደመራ በዓል ተብሎ እንዲሁም መስከረም 17 ቀን የሚከበረዉ የመስቀል በዓል ጥንታዊነቱን ይዞ የቀጠለ የዐደባባይ በዓል በመሆኑ ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበቻቸዉ ቀርሶቻችን አንዱ ነው፡፡ የዐደባባይ በዓላቶቻችን የአብሮነት እሴቶቻችንን የሚያጎሉ፣ የብዝኃነታችን ጌጥነት ማሳያዎች ከመሆን ባሻገር የበርካታ ጎብኝዎችን ቀልብ የሚስቡ ሀብቶቻችን እየሆኑ መጥተዋል፡፡
መስከረም በርከት ያሉ በዓለት የምናከብርበት ወር ነው፤ ዛሬ እንኳ የመስቀል በዓልን ስናከብር የዓለም የቱሪዝም ቀንን ጭምር እያከበርን ነው፡፡ የዓለም ቱሪዝም ቀን በ1980 (እ.አ.አ) በተባበሩት መንግሥታት የዓለም ቱሪዝም ድርጅት ሐውልት መቆምን ምክንያት ተደርጎ የተመረጠ የቱሪዝም መታሰቢያ ቀን ነው፡፡
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0ZFexyc8JkA9T3VV5XN7gWhvoB3kbuKwYyL3Jgnm5vebfgbcqd6NqKQ5kfKLdDMhKl
👍15❤14
በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እየተከበረ የሚገኘው የደመራ በዓል በፎቶ
በአሰግድ ሲሳይ እና በናርዶስ አዳነ
#etv #EBC #ደመራ
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02WHRwhFHkxBWCoscmi9dZmZxHnNmhPw94ZnWnG7LhWPLBEXCDWaL9ftHw2nEx8gYTl
በአሰግድ ሲሳይ እና በናርዶስ አዳነ
#etv #EBC #ደመራ
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02WHRwhFHkxBWCoscmi9dZmZxHnNmhPw94ZnWnG7LhWPLBEXCDWaL9ftHw2nEx8gYTl
Facebook
Ethiopian Broadcasting Corporation
በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እየተከበረ የሚገኘው የደመራ በዓል በፎቶ
በአሰግድ ሲሳይ እና በናርዶስ አዳነ
#etv #EBC #ደመራ
በአሰግድ ሲሳይ እና በናርዶስ አዳነ
#etv #EBC #ደመራ
❤6👍4
የተራራው ላይ የዓጋመ መስቀል እና ደመራ
***********************
ኢትዮጵያ ውስጥ የመስቀል በአል በተለያዩ ቦታዎች በድምቀት ይከበራል።
በመስቀል በዓል ከቤተስብ እርቆ ያለ እረጅም መንገድ ተጉዞም ቢሆን ቤተሰቡን ይጠይቃል ናፍቆቱን ይወጣል ያለውን ስጦታም በዚሁ በዓል ያበረክታል።
ታዲያ ይህ ትልቅ ሀይማኖታዊ መሰረት ያለው ከቦታ ቦታ ደግሞ የማህበረሰቡ አንድነት ተጠብቆበት የቆየ ባህላዊ አንድምታን የተላበሰ በአል ሲነሳ የዓጋመ መስቀል አይረሳም።
በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል በትግራይ ክልል በአዲግራት ከተማ የሚከበረው የዓጋመ መስቀል እጅግ በድምቀት ከሚከበሩ እና የተለየ አከባበር ካላቸው የመስቀል በአላት አንዱ ነው። እርግጥ የበዓሉ አከባበር ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓቱ እንዳለ ቢሆንም ባሕላዊ ይዘትንም የተላበሰ ነው።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0QX92xsJgojge6sCpx9L3t3tZGUsx5StuNzhQVnGyY2BK71dD54AJDsC91xYt11Vyl
***********************
ኢትዮጵያ ውስጥ የመስቀል በአል በተለያዩ ቦታዎች በድምቀት ይከበራል።
በመስቀል በዓል ከቤተስብ እርቆ ያለ እረጅም መንገድ ተጉዞም ቢሆን ቤተሰቡን ይጠይቃል ናፍቆቱን ይወጣል ያለውን ስጦታም በዚሁ በዓል ያበረክታል።
ታዲያ ይህ ትልቅ ሀይማኖታዊ መሰረት ያለው ከቦታ ቦታ ደግሞ የማህበረሰቡ አንድነት ተጠብቆበት የቆየ ባህላዊ አንድምታን የተላበሰ በአል ሲነሳ የዓጋመ መስቀል አይረሳም።
በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል በትግራይ ክልል በአዲግራት ከተማ የሚከበረው የዓጋመ መስቀል እጅግ በድምቀት ከሚከበሩ እና የተለየ አከባበር ካላቸው የመስቀል በአላት አንዱ ነው። እርግጥ የበዓሉ አከባበር ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓቱ እንዳለ ቢሆንም ባሕላዊ ይዘትንም የተላበሰ ነው።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0QX92xsJgojge6sCpx9L3t3tZGUsx5StuNzhQVnGyY2BK71dD54AJDsC91xYt11Vyl
❤11👍10
ዓለም የእኔም ነው ብሎ የመስቀል በዓልን በቅርስነት ከመዘገበው 11 ዓመታት ተቆጠሩ
*****************
የመስቀል በዓል አከባበር ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበቻቸው ቅርሶች መካከል የመጀመሪያው በዩኒስኮ የተመዘገበ የማይዳሰስ ቅርስ ነው።
ልክ የዛሬ 11 ዓመት ህዳር 2006 ዓ.ም ኢትዮጵያ ተንከባክባ እና ጠብቃ ይዛው የነበረው በዓል የዓለምም በዓል ይሆን ዘንድ ነው የተመዘገበው።
የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ የማይዳሰስ ቅርስ (Intangible) ሆኖ የተመዘገበው በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ በተደረገ ስምንተኛው የዩኔስኮ የማይዳሰሱ ቅርሶች ጉባዔ ላይ ነበረ።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid04hV4BPDBrmgdSNmR7RH8tcs8qfsicSzoh6zNABUeywDE6CX8h4ZQJCD4eLnEHu7cl
*****************
የመስቀል በዓል አከባበር ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበቻቸው ቅርሶች መካከል የመጀመሪያው በዩኒስኮ የተመዘገበ የማይዳሰስ ቅርስ ነው።
ልክ የዛሬ 11 ዓመት ህዳር 2006 ዓ.ም ኢትዮጵያ ተንከባክባ እና ጠብቃ ይዛው የነበረው በዓል የዓለምም በዓል ይሆን ዘንድ ነው የተመዘገበው።
የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ የማይዳሰስ ቅርስ (Intangible) ሆኖ የተመዘገበው በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ በተደረገ ስምንተኛው የዩኔስኮ የማይዳሰሱ ቅርሶች ጉባዔ ላይ ነበረ።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid04hV4BPDBrmgdSNmR7RH8tcs8qfsicSzoh6zNABUeywDE6CX8h4ZQJCD4eLnEHu7cl
👍13❤10👎2
አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከግሪክና ሴራሊዮን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ
*******************
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ኢትዮጵያ ከግሪክ እና ሴራሊዮን ጋር ያላትን ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ዙሪያ ከሁለቱ አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያይተዋል።
ሚኒስትሩ ከግሪኩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጊኦርጎስ ጀርፐትራይተስ ጋር ባደረጉት ውይይት ግሪክ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት አባል ሆና በመመረጧ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።
አምባሳደር ታዬ በወቅታዊው የአፍሪካ ቀንድ ጉዳይ ላይ ለሚኒስትሩ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ፀረ-ሽብር ዘመቻ አጠናክራ ለመቀጠል ያላትን ቁርጠኝነት ገልፀዋል።
በተያያዘ አምባሳደር ታዬ ከሴራሊዮን ውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ጢሞቲ ካባ ጋር በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና ደኀንነት ዙሪያ መክረዋል።
በውይይቱ ላይም አምባሳደር ታዬ፤ በሶማሊያ ከድህረ አትሚስ በኋላ የሚኖረው የኃይል ሥምሪት ጊዜ ተወስዶ በጥንቃቄ መከናወን እንዳለበት መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
*******************
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ኢትዮጵያ ከግሪክ እና ሴራሊዮን ጋር ያላትን ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ዙሪያ ከሁለቱ አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያይተዋል።
ሚኒስትሩ ከግሪኩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጊኦርጎስ ጀርፐትራይተስ ጋር ባደረጉት ውይይት ግሪክ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት አባል ሆና በመመረጧ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።
አምባሳደር ታዬ በወቅታዊው የአፍሪካ ቀንድ ጉዳይ ላይ ለሚኒስትሩ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ፀረ-ሽብር ዘመቻ አጠናክራ ለመቀጠል ያላትን ቁርጠኝነት ገልፀዋል።
በተያያዘ አምባሳደር ታዬ ከሴራሊዮን ውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ጢሞቲ ካባ ጋር በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና ደኀንነት ዙሪያ መክረዋል።
በውይይቱ ላይም አምባሳደር ታዬ፤ በሶማሊያ ከድህረ አትሚስ በኋላ የሚኖረው የኃይል ሥምሪት ጊዜ ተወስዶ በጥንቃቄ መከናወን እንዳለበት መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
👍12❤11