EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) – Telegram
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
138K subscribers
38.3K photos
462 videos
80 files
13.1K links
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) @etvafaanoromoo1
@ETVkidschannel
@EBCWORLD1
@etventertainment1
Download Telegram
በ8 ዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄደው የኦዳ ቡሉ ስርዓት እየተካሄደ ነው
*****************

የቦረና ኦሮሞ የገዳ ስርዓት አካል የሆነውና በ8 ዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄደው የኦዳ ቡሉ ስርዓት እየተካሄደ ነው።

71ኛው የቦረና አባገዳ ኩራ ጃርሶ የስልጣን ርክክብ ቅድመ ዝግጅት የሆነው የኦዳ ቡሉ ስርዓት ላለፉት 27 ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች ቆይቷል።

በርካቶች ተሳታፊ የሆኑበት የመጨረሻዋ 27ኛ ቀን ላይ የተለያዩ ስነ-ስርዓቶች እየተካሄዱ ይገኛል።

የምርቃትና የዕርድ ስነ ስርዓት ከተካሄዱ ስርዓቶች መካከል ነው።

የኦዳ ቡሉ ስርዓት በቦረና የገዳ ስርዓት 8ኛ የስልጣን መጠናቀቂያ የሚደረግ ሲሆን ይህም ፈጣሪ የሚለመንበት ስርዓት መሆኑ ተገልጿል።

በስነ ስርዓቱ መሰረት ከ3 ወር በኋላ ባሊ ወይም የስልጣን ርክክብ ይካሄዳል።

በሙሉ ግርማይ
👍278👎2
የበሰቃ ሐይቅ ምሥጢሮች፦ራዕይን መከተል የማያወላውል ቁርጠኝነት እና ዓላማ ያለው ርምጃ ይጠይቃል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
👍51👏112
አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ የጎዴ ሼክ ኢብራሂም አብደላ አጠቃላይ ሆስፒታልን መርቀው ከፈቱ
****************

የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ በ300 ሚልዮን ብር ወጪ ማስፋፊያ የተደረገለት የጎዴ ከተማ ሼክ ኢብራሂም አብደላ አጠቃላይ ሆስፒታል እና አዲስ የተገነባውን የኦክስጂን ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሆስፒታሉና የኦክሲጂን ማምረቻ ማዕከሉ ከሚሰጡት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ባሻገር መንግሥት ለክልሉ የጤና ዘርፍ መሻሻል እያደረገ ያለውን ጥረት የሚያሳይ ነው ብለዋል።

ሆስፒታሉና የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጎዴ ከተማ ሥር የሚገኙ የጤና ማዕከላትን ጨምሮ በሸቤሌና አጎራባች ዞኖች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የጎላ ጠቀሜታን ያበረክታል ያሉት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሳ አህመድ ናቸው።

የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከል ቀጥሎ በክልሉ ሁለተኛው እንደሆነና በቀን 150 ሲሊንደሮችን የማምረት አቅም እንዳለውም ዶ/ር ሙሳ አክለው ገልፀዋል።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0gA3Z1nant8HNcACtfvhXhzArzDghwQmN7aK3ZgaGNMtzhNsHciyEvXYmYm3Va6Frl
👍3515