ህብረተሰቡ ለሰላምና ለልማት ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ርዕስ መስተዳደር አረጋ ከበደ ገለፁ
*******************
የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር አረጋ ከበደ ከጎንደር ከተማ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
አሁን እየተከናወነ ያለው ልማት የበለጠ እንዲስፋፋና በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ከከተማ፣ ከክልልና ከፌዴራል መንግሥት ጋር በመቀናጀት በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል አስገንዝበዋል።
ሰላም በመንግሥት ተፈጥራ በመንግሥት ተባርካ የምትቀርብ መና አይደለችም ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ሰላም የሁሉን ትብብርና ቅንጅት ትፈልጋለች ብለዋል።
አሁን ያለውን አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማፅናት ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
የጎንደርን ገፅታ ሊያሳምሩ የሚያስችሉ ትልልቅ ስራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆኑን በመገንዘብ ልማቱ ለማስቀጠል ሰላምን ማስፈን እንደሚገባ ተናግረዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው በበኩላቸው፤ አሁን ያሉ የልማት እድሎችን ለመጠቀም ሰላምን ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል።
ከህዝቡ ጋር በመደጋገፍና በመመካከር በመስራት ከቻልን በአጭር ጊዜ ጎንደር ከተማን ሊመጥን የሚችል ልማት ማምጣት እንደሚቻል መናገራቸውን የጎንደር ከተማ ኮሙዩኒኬሽ ቢሮ መረጃ አመልክቷል።
*******************
የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር አረጋ ከበደ ከጎንደር ከተማ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
አሁን እየተከናወነ ያለው ልማት የበለጠ እንዲስፋፋና በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ከከተማ፣ ከክልልና ከፌዴራል መንግሥት ጋር በመቀናጀት በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል አስገንዝበዋል።
ሰላም በመንግሥት ተፈጥራ በመንግሥት ተባርካ የምትቀርብ መና አይደለችም ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ሰላም የሁሉን ትብብርና ቅንጅት ትፈልጋለች ብለዋል።
አሁን ያለውን አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማፅናት ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
የጎንደርን ገፅታ ሊያሳምሩ የሚያስችሉ ትልልቅ ስራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆኑን በመገንዘብ ልማቱ ለማስቀጠል ሰላምን ማስፈን እንደሚገባ ተናግረዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው በበኩላቸው፤ አሁን ያሉ የልማት እድሎችን ለመጠቀም ሰላምን ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል።
ከህዝቡ ጋር በመደጋገፍና በመመካከር በመስራት ከቻልን በአጭር ጊዜ ጎንደር ከተማን ሊመጥን የሚችል ልማት ማምጣት እንደሚቻል መናገራቸውን የጎንደር ከተማ ኮሙዩኒኬሽ ቢሮ መረጃ አመልክቷል።
👍25❤5
በ8 ዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄደው የኦዳ ቡሉ ስርዓት እየተካሄደ ነው
*****************
የቦረና ኦሮሞ የገዳ ስርዓት አካል የሆነውና በ8 ዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄደው የኦዳ ቡሉ ስርዓት እየተካሄደ ነው።
71ኛው የቦረና አባገዳ ኩራ ጃርሶ የስልጣን ርክክብ ቅድመ ዝግጅት የሆነው የኦዳ ቡሉ ስርዓት ላለፉት 27 ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች ቆይቷል።
በርካቶች ተሳታፊ የሆኑበት የመጨረሻዋ 27ኛ ቀን ላይ የተለያዩ ስነ-ስርዓቶች እየተካሄዱ ይገኛል።
የምርቃትና የዕርድ ስነ ስርዓት ከተካሄዱ ስርዓቶች መካከል ነው።
የኦዳ ቡሉ ስርዓት በቦረና የገዳ ስርዓት 8ኛ የስልጣን መጠናቀቂያ የሚደረግ ሲሆን ይህም ፈጣሪ የሚለመንበት ስርዓት መሆኑ ተገልጿል።
በስነ ስርዓቱ መሰረት ከ3 ወር በኋላ ባሊ ወይም የስልጣን ርክክብ ይካሄዳል።
በሙሉ ግርማይ
*****************
የቦረና ኦሮሞ የገዳ ስርዓት አካል የሆነውና በ8 ዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄደው የኦዳ ቡሉ ስርዓት እየተካሄደ ነው።
71ኛው የቦረና አባገዳ ኩራ ጃርሶ የስልጣን ርክክብ ቅድመ ዝግጅት የሆነው የኦዳ ቡሉ ስርዓት ላለፉት 27 ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች ቆይቷል።
በርካቶች ተሳታፊ የሆኑበት የመጨረሻዋ 27ኛ ቀን ላይ የተለያዩ ስነ-ስርዓቶች እየተካሄዱ ይገኛል።
የምርቃትና የዕርድ ስነ ስርዓት ከተካሄዱ ስርዓቶች መካከል ነው።
የኦዳ ቡሉ ስርዓት በቦረና የገዳ ስርዓት 8ኛ የስልጣን መጠናቀቂያ የሚደረግ ሲሆን ይህም ፈጣሪ የሚለመንበት ስርዓት መሆኑ ተገልጿል።
በስነ ስርዓቱ መሰረት ከ3 ወር በኋላ ባሊ ወይም የስልጣን ርክክብ ይካሄዳል።
በሙሉ ግርማይ
👍27❤8👎2
የበሰቃ ሐይቅ ምሥጢሮች፦ራዕይን መከተል የማያወላውል ቁርጠኝነት እና ዓላማ ያለው ርምጃ ይጠይቃል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
👍51👏11❤2
አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ የጎዴ ሼክ ኢብራሂም አብደላ አጠቃላይ ሆስፒታልን መርቀው ከፈቱ
****************
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ በ300 ሚልዮን ብር ወጪ ማስፋፊያ የተደረገለት የጎዴ ከተማ ሼክ ኢብራሂም አብደላ አጠቃላይ ሆስፒታል እና አዲስ የተገነባውን የኦክስጂን ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሆስፒታሉና የኦክሲጂን ማምረቻ ማዕከሉ ከሚሰጡት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ባሻገር መንግሥት ለክልሉ የጤና ዘርፍ መሻሻል እያደረገ ያለውን ጥረት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ሆስፒታሉና የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጎዴ ከተማ ሥር የሚገኙ የጤና ማዕከላትን ጨምሮ በሸቤሌና አጎራባች ዞኖች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የጎላ ጠቀሜታን ያበረክታል ያሉት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሳ አህመድ ናቸው።
የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከል ቀጥሎ በክልሉ ሁለተኛው እንደሆነና በቀን 150 ሲሊንደሮችን የማምረት አቅም እንዳለውም ዶ/ር ሙሳ አክለው ገልፀዋል።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0gA3Z1nant8HNcACtfvhXhzArzDghwQmN7aK3ZgaGNMtzhNsHciyEvXYmYm3Va6Frl
****************
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ በ300 ሚልዮን ብር ወጪ ማስፋፊያ የተደረገለት የጎዴ ከተማ ሼክ ኢብራሂም አብደላ አጠቃላይ ሆስፒታል እና አዲስ የተገነባውን የኦክስጂን ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሆስፒታሉና የኦክሲጂን ማምረቻ ማዕከሉ ከሚሰጡት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ባሻገር መንግሥት ለክልሉ የጤና ዘርፍ መሻሻል እያደረገ ያለውን ጥረት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ሆስፒታሉና የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጎዴ ከተማ ሥር የሚገኙ የጤና ማዕከላትን ጨምሮ በሸቤሌና አጎራባች ዞኖች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የጎላ ጠቀሜታን ያበረክታል ያሉት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሳ አህመድ ናቸው።
የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከል ቀጥሎ በክልሉ ሁለተኛው እንደሆነና በቀን 150 ሲሊንደሮችን የማምረት አቅም እንዳለውም ዶ/ር ሙሳ አክለው ገልፀዋል።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0gA3Z1nant8HNcACtfvhXhzArzDghwQmN7aK3ZgaGNMtzhNsHciyEvXYmYm3Va6Frl
👍35❤15