የበሰቃ ሐይቅ ምሥጢሮች፦ራዕይን መከተል የማያወላውል ቁርጠኝነት እና ዓላማ ያለው ርምጃ ይጠይቃል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
👍51👏11❤2
አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ የጎዴ ሼክ ኢብራሂም አብደላ አጠቃላይ ሆስፒታልን መርቀው ከፈቱ
****************
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ በ300 ሚልዮን ብር ወጪ ማስፋፊያ የተደረገለት የጎዴ ከተማ ሼክ ኢብራሂም አብደላ አጠቃላይ ሆስፒታል እና አዲስ የተገነባውን የኦክስጂን ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሆስፒታሉና የኦክሲጂን ማምረቻ ማዕከሉ ከሚሰጡት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ባሻገር መንግሥት ለክልሉ የጤና ዘርፍ መሻሻል እያደረገ ያለውን ጥረት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ሆስፒታሉና የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጎዴ ከተማ ሥር የሚገኙ የጤና ማዕከላትን ጨምሮ በሸቤሌና አጎራባች ዞኖች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የጎላ ጠቀሜታን ያበረክታል ያሉት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሳ አህመድ ናቸው።
የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከል ቀጥሎ በክልሉ ሁለተኛው እንደሆነና በቀን 150 ሲሊንደሮችን የማምረት አቅም እንዳለውም ዶ/ር ሙሳ አክለው ገልፀዋል።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0gA3Z1nant8HNcACtfvhXhzArzDghwQmN7aK3ZgaGNMtzhNsHciyEvXYmYm3Va6Frl
****************
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ በ300 ሚልዮን ብር ወጪ ማስፋፊያ የተደረገለት የጎዴ ከተማ ሼክ ኢብራሂም አብደላ አጠቃላይ ሆስፒታል እና አዲስ የተገነባውን የኦክስጂን ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሆስፒታሉና የኦክሲጂን ማምረቻ ማዕከሉ ከሚሰጡት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ባሻገር መንግሥት ለክልሉ የጤና ዘርፍ መሻሻል እያደረገ ያለውን ጥረት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ሆስፒታሉና የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጎዴ ከተማ ሥር የሚገኙ የጤና ማዕከላትን ጨምሮ በሸቤሌና አጎራባች ዞኖች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የጎላ ጠቀሜታን ያበረክታል ያሉት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሳ አህመድ ናቸው።
የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከል ቀጥሎ በክልሉ ሁለተኛው እንደሆነና በቀን 150 ሲሊንደሮችን የማምረት አቅም እንዳለውም ዶ/ር ሙሳ አክለው ገልፀዋል።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0gA3Z1nant8HNcACtfvhXhzArzDghwQmN7aK3ZgaGNMtzhNsHciyEvXYmYm3Va6Frl
👍35❤15
ነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ፈጠራ ውድድር።
ሃሳብ ወደ ተግባር እንዲለወጥ ባደረገው ነጋድራስ የስራ ፈጠራ ውድድር ከምዕራፍ ሶስት ጀምሮ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችል የታይትል ስፖንሰርሺፕ ስምምነት ተፈርሟል፡፡
ኢቢሲ ወደ ይዘት በሚያደርገው ጉዞ ውስጥ ከይዘት ስራዎች አንዱ የሆነው ነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የስራ ፈጠራ ውድድር ከህዳር 1 ጀምሮ ይቀርባል፡፡
አዳዲስ የስራ ፈጠራ ሃሳቦች ወደ ፊት እንዲመጡና በሀገር ኢኮኖሚ ላይም ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ ኢቢሲ ሁልጊዜም ኃላፊነቱን ይወጣል፡፡
ከሀገር ልማት ጀርባ ያለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዚህ ፕሮግራም የታይትል ስፖንሰርሽፕ ስምምነትን ከኢትዮጰያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ከማድረግ ባለፈ ስራ ፈጣሪዎችን ለመደገፍ ቁርጠኝነቱን በተግባር አሳይቷል።
በስምምነቱ መሠረት የውድድሩ ሽልማት ወደ ላቀ ደረጃ የተሸጋገረ ሲሆን አሸናፊዎች ከሚያገኙት የገንዘብ ሽልማት በተጨማሪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ማስጀመሪያ የገንዘብ ብድር ያለማስያዣ የሚያገኙ ይሆናል፡፡
ነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ፈጠራ ውድድር ከእሁድ ህዳር 1 ቀን 2017 ጀምሮ ከቀኑ 8 ሰዓት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዜና ቻናል በየሳምንቱ ይቀርባል፡፡
#etv #EBC #cbe #የኢትዮጵያንግድባንክ #ነጋድራስ #CBE #Ethiopian #Commercial_bank_of_Ethiopia #Ethiopia #ኢትዮጵያ #ስራፈጠራ #ነጋድራስ_የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ_የሥራ_ፈጠራ_ውድድር #negadras
ሃሳብ ወደ ተግባር እንዲለወጥ ባደረገው ነጋድራስ የስራ ፈጠራ ውድድር ከምዕራፍ ሶስት ጀምሮ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችል የታይትል ስፖንሰርሺፕ ስምምነት ተፈርሟል፡፡
ኢቢሲ ወደ ይዘት በሚያደርገው ጉዞ ውስጥ ከይዘት ስራዎች አንዱ የሆነው ነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የስራ ፈጠራ ውድድር ከህዳር 1 ጀምሮ ይቀርባል፡፡
አዳዲስ የስራ ፈጠራ ሃሳቦች ወደ ፊት እንዲመጡና በሀገር ኢኮኖሚ ላይም ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ ኢቢሲ ሁልጊዜም ኃላፊነቱን ይወጣል፡፡
ከሀገር ልማት ጀርባ ያለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዚህ ፕሮግራም የታይትል ስፖንሰርሽፕ ስምምነትን ከኢትዮጰያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ከማድረግ ባለፈ ስራ ፈጣሪዎችን ለመደገፍ ቁርጠኝነቱን በተግባር አሳይቷል።
በስምምነቱ መሠረት የውድድሩ ሽልማት ወደ ላቀ ደረጃ የተሸጋገረ ሲሆን አሸናፊዎች ከሚያገኙት የገንዘብ ሽልማት በተጨማሪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ማስጀመሪያ የገንዘብ ብድር ያለማስያዣ የሚያገኙ ይሆናል፡፡
ነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ፈጠራ ውድድር ከእሁድ ህዳር 1 ቀን 2017 ጀምሮ ከቀኑ 8 ሰዓት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዜና ቻናል በየሳምንቱ ይቀርባል፡፡
#etv #EBC #cbe #የኢትዮጵያንግድባንክ #ነጋድራስ #CBE #Ethiopian #Commercial_bank_of_Ethiopia #Ethiopia #ኢትዮጵያ #ስራፈጠራ #ነጋድራስ_የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ_የሥራ_ፈጠራ_ውድድር #negadras
👍25❤2👏1
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከሩሲያ አቻቸው ጋር ተወያዩ
********************
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከሩሲያ አቻቸው ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሚኒስሮቹ ውይይቱን ያካሄዱት ከመጀመሪያው የሩሲያ አፍሪካ የሚኒስትሮች አጋርነት ፎረም ጎን ለጎን ነው፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት አግባብ ላይ መምከራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
********************
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከሩሲያ አቻቸው ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሚኒስሮቹ ውይይቱን ያካሄዱት ከመጀመሪያው የሩሲያ አፍሪካ የሚኒስትሮች አጋርነት ፎረም ጎን ለጎን ነው፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት አግባብ ላይ መምከራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
👍23❤6
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ እና የሁርሶ ዕጩ መኮንን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የወልወል ድህረ-ምረቃ እና የ25ኛ ሰላም ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ነው
**********************
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ እና የሁርሶ ዕጩ መኮንን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የወልወል ድህረ-ምረቃ እና የ25ኛ ሰላም ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ይገኛል።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ ጄኔራል መኮንኖች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ተመራቂ ዕጩ መኮንኖች በማሠልጠኛ ማዕከሉ ስልጠናቸውን ሲከታተሉ የቆዩና የሚጠበቅባቸውን ሥልጠና ወስደው ያለፉ መሆናቸው ተገልጿል።
ይመር አደም
**********************
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ እና የሁርሶ ዕጩ መኮንን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የወልወል ድህረ-ምረቃ እና የ25ኛ ሰላም ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ይገኛል።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ ጄኔራል መኮንኖች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ተመራቂ ዕጩ መኮንኖች በማሠልጠኛ ማዕከሉ ስልጠናቸውን ሲከታተሉ የቆዩና የሚጠበቅባቸውን ሥልጠና ወስደው ያለፉ መሆናቸው ተገልጿል።
ይመር አደም
👍19❤12👏3👎2