በ8 ዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄደው የኦዳ ቡሉ ስርዓት እየተካሄደ ነው
*****************
የቦረና ኦሮሞ የገዳ ስርዓት አካል የሆነውና በ8 ዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄደው የኦዳ ቡሉ ስርዓት እየተካሄደ ነው።
71ኛው የቦረና አባገዳ ኩራ ጃርሶ የስልጣን ርክክብ ቅድመ ዝግጅት የሆነው የኦዳ ቡሉ ስርዓት ላለፉት 27 ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች ቆይቷል።
በርካቶች ተሳታፊ የሆኑበት የመጨረሻዋ 27ኛ ቀን ላይ የተለያዩ ስነ-ስርዓቶች እየተካሄዱ ይገኛል።
የምርቃትና የዕርድ ስነ ስርዓት ከተካሄዱ ስርዓቶች መካከል ነው።
የኦዳ ቡሉ ስርዓት በቦረና የገዳ ስርዓት 8ኛ የስልጣን መጠናቀቂያ የሚደረግ ሲሆን ይህም ፈጣሪ የሚለመንበት ስርዓት መሆኑ ተገልጿል።
በስነ ስርዓቱ መሰረት ከ3 ወር በኋላ ባሊ ወይም የስልጣን ርክክብ ይካሄዳል።
በሙሉ ግርማይ
*****************
የቦረና ኦሮሞ የገዳ ስርዓት አካል የሆነውና በ8 ዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄደው የኦዳ ቡሉ ስርዓት እየተካሄደ ነው።
71ኛው የቦረና አባገዳ ኩራ ጃርሶ የስልጣን ርክክብ ቅድመ ዝግጅት የሆነው የኦዳ ቡሉ ስርዓት ላለፉት 27 ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች ቆይቷል።
በርካቶች ተሳታፊ የሆኑበት የመጨረሻዋ 27ኛ ቀን ላይ የተለያዩ ስነ-ስርዓቶች እየተካሄዱ ይገኛል።
የምርቃትና የዕርድ ስነ ስርዓት ከተካሄዱ ስርዓቶች መካከል ነው።
የኦዳ ቡሉ ስርዓት በቦረና የገዳ ስርዓት 8ኛ የስልጣን መጠናቀቂያ የሚደረግ ሲሆን ይህም ፈጣሪ የሚለመንበት ስርዓት መሆኑ ተገልጿል።
በስነ ስርዓቱ መሰረት ከ3 ወር በኋላ ባሊ ወይም የስልጣን ርክክብ ይካሄዳል።
በሙሉ ግርማይ
👍27❤8👎2
የበሰቃ ሐይቅ ምሥጢሮች፦ራዕይን መከተል የማያወላውል ቁርጠኝነት እና ዓላማ ያለው ርምጃ ይጠይቃል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
👍51👏11❤2
አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ የጎዴ ሼክ ኢብራሂም አብደላ አጠቃላይ ሆስፒታልን መርቀው ከፈቱ
****************
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ በ300 ሚልዮን ብር ወጪ ማስፋፊያ የተደረገለት የጎዴ ከተማ ሼክ ኢብራሂም አብደላ አጠቃላይ ሆስፒታል እና አዲስ የተገነባውን የኦክስጂን ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሆስፒታሉና የኦክሲጂን ማምረቻ ማዕከሉ ከሚሰጡት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ባሻገር መንግሥት ለክልሉ የጤና ዘርፍ መሻሻል እያደረገ ያለውን ጥረት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ሆስፒታሉና የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጎዴ ከተማ ሥር የሚገኙ የጤና ማዕከላትን ጨምሮ በሸቤሌና አጎራባች ዞኖች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የጎላ ጠቀሜታን ያበረክታል ያሉት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሳ አህመድ ናቸው።
የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከል ቀጥሎ በክልሉ ሁለተኛው እንደሆነና በቀን 150 ሲሊንደሮችን የማምረት አቅም እንዳለውም ዶ/ር ሙሳ አክለው ገልፀዋል።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0gA3Z1nant8HNcACtfvhXhzArzDghwQmN7aK3ZgaGNMtzhNsHciyEvXYmYm3Va6Frl
****************
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ በ300 ሚልዮን ብር ወጪ ማስፋፊያ የተደረገለት የጎዴ ከተማ ሼክ ኢብራሂም አብደላ አጠቃላይ ሆስፒታል እና አዲስ የተገነባውን የኦክስጂን ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ሆስፒታሉና የኦክሲጂን ማምረቻ ማዕከሉ ከሚሰጡት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ባሻገር መንግሥት ለክልሉ የጤና ዘርፍ መሻሻል እያደረገ ያለውን ጥረት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ሆስፒታሉና የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጎዴ ከተማ ሥር የሚገኙ የጤና ማዕከላትን ጨምሮ በሸቤሌና አጎራባች ዞኖች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የጎላ ጠቀሜታን ያበረክታል ያሉት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሳ አህመድ ናቸው።
የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከሉ በጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው የኦክስጂን ማምረቻ ማዕከል ቀጥሎ በክልሉ ሁለተኛው እንደሆነና በቀን 150 ሲሊንደሮችን የማምረት አቅም እንዳለውም ዶ/ር ሙሳ አክለው ገልፀዋል።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0gA3Z1nant8HNcACtfvhXhzArzDghwQmN7aK3ZgaGNMtzhNsHciyEvXYmYm3Va6Frl
👍35❤15
ነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ፈጠራ ውድድር።
ሃሳብ ወደ ተግባር እንዲለወጥ ባደረገው ነጋድራስ የስራ ፈጠራ ውድድር ከምዕራፍ ሶስት ጀምሮ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችል የታይትል ስፖንሰርሺፕ ስምምነት ተፈርሟል፡፡
ኢቢሲ ወደ ይዘት በሚያደርገው ጉዞ ውስጥ ከይዘት ስራዎች አንዱ የሆነው ነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የስራ ፈጠራ ውድድር ከህዳር 1 ጀምሮ ይቀርባል፡፡
አዳዲስ የስራ ፈጠራ ሃሳቦች ወደ ፊት እንዲመጡና በሀገር ኢኮኖሚ ላይም ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ ኢቢሲ ሁልጊዜም ኃላፊነቱን ይወጣል፡፡
ከሀገር ልማት ጀርባ ያለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዚህ ፕሮግራም የታይትል ስፖንሰርሽፕ ስምምነትን ከኢትዮጰያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ከማድረግ ባለፈ ስራ ፈጣሪዎችን ለመደገፍ ቁርጠኝነቱን በተግባር አሳይቷል።
በስምምነቱ መሠረት የውድድሩ ሽልማት ወደ ላቀ ደረጃ የተሸጋገረ ሲሆን አሸናፊዎች ከሚያገኙት የገንዘብ ሽልማት በተጨማሪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ማስጀመሪያ የገንዘብ ብድር ያለማስያዣ የሚያገኙ ይሆናል፡፡
ነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ፈጠራ ውድድር ከእሁድ ህዳር 1 ቀን 2017 ጀምሮ ከቀኑ 8 ሰዓት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዜና ቻናል በየሳምንቱ ይቀርባል፡፡
#etv #EBC #cbe #የኢትዮጵያንግድባንክ #ነጋድራስ #CBE #Ethiopian #Commercial_bank_of_Ethiopia #Ethiopia #ኢትዮጵያ #ስራፈጠራ #ነጋድራስ_የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ_የሥራ_ፈጠራ_ውድድር #negadras
ሃሳብ ወደ ተግባር እንዲለወጥ ባደረገው ነጋድራስ የስራ ፈጠራ ውድድር ከምዕራፍ ሶስት ጀምሮ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችል የታይትል ስፖንሰርሺፕ ስምምነት ተፈርሟል፡፡
ኢቢሲ ወደ ይዘት በሚያደርገው ጉዞ ውስጥ ከይዘት ስራዎች አንዱ የሆነው ነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የስራ ፈጠራ ውድድር ከህዳር 1 ጀምሮ ይቀርባል፡፡
አዳዲስ የስራ ፈጠራ ሃሳቦች ወደ ፊት እንዲመጡና በሀገር ኢኮኖሚ ላይም ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ ኢቢሲ ሁልጊዜም ኃላፊነቱን ይወጣል፡፡
ከሀገር ልማት ጀርባ ያለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዚህ ፕሮግራም የታይትል ስፖንሰርሽፕ ስምምነትን ከኢትዮጰያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ከማድረግ ባለፈ ስራ ፈጣሪዎችን ለመደገፍ ቁርጠኝነቱን በተግባር አሳይቷል።
በስምምነቱ መሠረት የውድድሩ ሽልማት ወደ ላቀ ደረጃ የተሸጋገረ ሲሆን አሸናፊዎች ከሚያገኙት የገንዘብ ሽልማት በተጨማሪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ማስጀመሪያ የገንዘብ ብድር ያለማስያዣ የሚያገኙ ይሆናል፡፡
ነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ፈጠራ ውድድር ከእሁድ ህዳር 1 ቀን 2017 ጀምሮ ከቀኑ 8 ሰዓት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዜና ቻናል በየሳምንቱ ይቀርባል፡፡
#etv #EBC #cbe #የኢትዮጵያንግድባንክ #ነጋድራስ #CBE #Ethiopian #Commercial_bank_of_Ethiopia #Ethiopia #ኢትዮጵያ #ስራፈጠራ #ነጋድራስ_የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ_የሥራ_ፈጠራ_ውድድር #negadras
👍25❤2👏1
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከሩሲያ አቻቸው ጋር ተወያዩ
********************
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከሩሲያ አቻቸው ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሚኒስሮቹ ውይይቱን ያካሄዱት ከመጀመሪያው የሩሲያ አፍሪካ የሚኒስትሮች አጋርነት ፎረም ጎን ለጎን ነው፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት አግባብ ላይ መምከራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
********************
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከሩሲያ አቻቸው ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሚኒስሮቹ ውይይቱን ያካሄዱት ከመጀመሪያው የሩሲያ አፍሪካ የሚኒስትሮች አጋርነት ፎረም ጎን ለጎን ነው፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት አግባብ ላይ መምከራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
👍23❤6