"ጥቁር አደይ" ፊልም ሊመረቅ ነው
በደራሲ እና ዳይሬክተር ፍፁም ካሣሁን የተሰራው "ጥቁር አደይ" ፊልም የፊታችን ሐምሌ 10 2016 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል ተብሏል።
በፊልሙ ላይ ኤደን አይሸሹም፤ ካሣሁን ፍስሐ ማንዴላ፤ ናታን ጌታቸው፤ ነቢዩ እንድሪስ ጨምሮ ከ186 በላይ ተዋናያን እንደተሳተፉበት አዘጋጆቹ ለኤቨንት አዲስ ድረገፅ ተናግረዋል።
"ጥቁር አደይ" ፊልም አንድ ሰዓት ከሐምሳ ደቂቃ ረዝመት ያለው ሲሆን ከ6.7 ሚሊየን ብር በላይ ውጪ እንደወጣበት ተነግሯል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በደራሲ እና ዳይሬክተር ፍፁም ካሣሁን የተሰራው "ጥቁር አደይ" ፊልም የፊታችን ሐምሌ 10 2016 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል ተብሏል።
በፊልሙ ላይ ኤደን አይሸሹም፤ ካሣሁን ፍስሐ ማንዴላ፤ ናታን ጌታቸው፤ ነቢዩ እንድሪስ ጨምሮ ከ186 በላይ ተዋናያን እንደተሳተፉበት አዘጋጆቹ ለኤቨንት አዲስ ድረገፅ ተናግረዋል።
"ጥቁር አደይ" ፊልም አንድ ሰዓት ከሐምሳ ደቂቃ ረዝመት ያለው ሲሆን ከ6.7 ሚሊየን ብር በላይ ውጪ እንደወጣበት ተነግሯል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"የሚስቶቼ ባሎች" ተውኔት በዓለም ሲኒማ መቅረብ ከጀመረ አንድ ዓመት እንደሞላው አዘጋጆቹ አስታወቁ
በአበባየሁ ታደሰ ተደርሶ በተስፋዬ ገ/ማርያምና ይገረም ደጀኔ (አስቴር ) የተዘጋጀው "የሚስቶቼ ባሎች" ኮሜዲ ተውኔት በዓለም ሲኒማ መቅረብ ከጀመረ አንድ ዓመት እንደሞላው አዘጋጆቹ ለኤቨንት አዲስ ድረገፅ ተናገረዋል።
አዘጋጆቹ "የዛሬ ዓመት ሰኔ 21 የተከፈተው "የሚስቶቼ ባሎች" በተወዳጅነቱ እንደዘለቀ ይኸው አንድ ዓመት ሞላው።ረቡዕ በ12:00 ሰዓት ብቅ ብለው እየተዝናኑ አንደኛ ዓመታችንን ከእኛ ጋር ያክብሩ" ያሉ ሲሆን
በተጨማሪም "የሚስቶቼ ባሎች" ተውኔት ዘወትር ረቡዕ በ12:00 ሰዓት በዓለም ሲኒማ መታየቱን ይቀጥላል " ብለዋል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በአበባየሁ ታደሰ ተደርሶ በተስፋዬ ገ/ማርያምና ይገረም ደጀኔ (አስቴር ) የተዘጋጀው "የሚስቶቼ ባሎች" ኮሜዲ ተውኔት በዓለም ሲኒማ መቅረብ ከጀመረ አንድ ዓመት እንደሞላው አዘጋጆቹ ለኤቨንት አዲስ ድረገፅ ተናገረዋል።
አዘጋጆቹ "የዛሬ ዓመት ሰኔ 21 የተከፈተው "የሚስቶቼ ባሎች" በተወዳጅነቱ እንደዘለቀ ይኸው አንድ ዓመት ሞላው።ረቡዕ በ12:00 ሰዓት ብቅ ብለው እየተዝናኑ አንደኛ ዓመታችንን ከእኛ ጋር ያክብሩ" ያሉ ሲሆን
በተጨማሪም "የሚስቶቼ ባሎች" ተውኔት ዘወትር ረቡዕ በ12:00 ሰዓት በዓለም ሲኒማ መታየቱን ይቀጥላል " ብለዋል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ታላቁ የጥበብ ሰው ነብይ መኮንን አረፈ
አንጋፋው ጋዜጠኛ፣ ደራሲ ፣ ገጣሚ እና ትርጓሜ ነብይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ አዲስ አድማስ ጋዜጣ አስታውቋል።
ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ባደረበት ህመም ህክምና ሲከታተል ቆይቶ፣ ድንገት ያረፈው ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ረፋዱ ላይ ነው።
አንጋፋው ጋዜጠኛ ነብይ መኮንን ለረጅም ዓመታት የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል።
ነብይ መኮንን ከአዲስ አድማስ መሥራቾች አንዱ ሲሆን በዋና አዘጋጅነት ጋዜጣዋን በመምራት ተወዳጅ ካደረጓት በቀዳሚነት ስሙ ይጠቀሳል።
"ነገም ሌላ ቀን ነው" "የመጨረሻው ንግግር" እና "የእኛ ሰው በአሜሪካ" የተሰኙ መጻሕፍትን ለአንባቢያን አድርሷል።
ኤቨንት አዲስ ድረገፅ በታላቁ የጥበብ ሰው ነብይ መኮንን ህልፈት ሀዘኑን ይገልጻል።ለቅርብ ቤተሰቦቹ፣ አድናቂዎቹ ከልብ መፅናናትን ይመኛል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አንጋፋው ጋዜጠኛ፣ ደራሲ ፣ ገጣሚ እና ትርጓሜ ነብይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ አዲስ አድማስ ጋዜጣ አስታውቋል።
ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ባደረበት ህመም ህክምና ሲከታተል ቆይቶ፣ ድንገት ያረፈው ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ረፋዱ ላይ ነው።
አንጋፋው ጋዜጠኛ ነብይ መኮንን ለረጅም ዓመታት የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል።
ነብይ መኮንን ከአዲስ አድማስ መሥራቾች አንዱ ሲሆን በዋና አዘጋጅነት ጋዜጣዋን በመምራት ተወዳጅ ካደረጓት በቀዳሚነት ስሙ ይጠቀሳል።
"ነገም ሌላ ቀን ነው" "የመጨረሻው ንግግር" እና "የእኛ ሰው በአሜሪካ" የተሰኙ መጻሕፍትን ለአንባቢያን አድርሷል።
ኤቨንት አዲስ ድረገፅ በታላቁ የጥበብ ሰው ነብይ መኮንን ህልፈት ሀዘኑን ይገልጻል።ለቅርብ ቤተሰቦቹ፣ አድናቂዎቹ ከልብ መፅናናትን ይመኛል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
Event Addis Media
ታላቁ የጥበብ ሰው ነብይ መኮንን አረፈ አንጋፋው ጋዜጠኛ፣ ደራሲ ፣ ገጣሚ እና ትርጓሜ ነብይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ አዲስ አድማስ ጋዜጣ አስታውቋል። ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ባደረበት ህመም ህክምና ሲከታተል ቆይቶ፣ ድንገት ያረፈው ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ረፋዱ ላይ ነው። አንጋፋው ጋዜጠኛ ነብይ መኮንን ለረጅም ዓመታት የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል።…
ስለ ነቢይ መኮንን አንዳንድ መረጃዎች
ታላቁ የጥበብ ሰው ነቢይ መኮንን ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 26 2016 ዓ.ም ማረፉ ተሰምቷል።ስለዚህ ግዙፍ ኢትዮጵያዊ የጥበብ ሰው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘውን መረጃ እንደሚከተለው ያቀርባል።
📍ነበይ መኮንን
አንጋፋ ጋዜጠኛ፣ ደራሲ ፣ ገጣሚ እና ትርጓሜ ነው።
📍ጋዜጠኛው ነቢይ መኮንን
-አንጋፋው ጋዜጠኛ ነቢይ መኮንን ለረጅም ዓመታት የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል።
-ነቢይ መኮንን ከአዲስ አድማስ መሥራቾች አንዱ ሲሆን በዋና አዘጋጅነት ጋዜጣዋን በመምራት ተወዳጅ ካደረጓት በቀዳሚነት ስሙ ይጠቀሳል።
📍ገጣሚው ነቢይ መኮንን
ገጣሚ ነቢይ መኮንን፤ “ስውር ስፌት” ቁጥር አንድና ሁለት፣ የግጥም መድበሎችን ጨምሮ በርካታ የግጥም ስራዎችን በተለያዩ መድረኮች በማቅረብ ይታወቃል፡፡
📍ደራሲው ነቢይ መኮንን
“የኛ ሰው በአሜሪካ” እና "የመጨረሻው ንግግር " የተሰኙ መጻሕፍቱ ዝነኛ ስራዎቹ ናቸው።
📍ተርጓሚው ነቢይ መኮንን
በአሜሪካዊቷ ደራሲ ማርጋሬት ሚሼል ተደርሶ፤ በመላው ዓለም ከፍተኛ ተነባቢነትን ያገኘውን “Gone With The Wind” የተሰኘውን ረጅም ልብ ወለድ መጽሐፍ በቁርጭራጭ የሲጋራ ወረቀቶች ላይ ተርጉሞ“ነገም ሌላ ቀን ነው” በሚል ርዕስ አስነብቧል፡፡
📍ተረት ጸሐፊው ነቢይ መኮንን
ነቢይ መኮንን ወደ 700 ገደማ ተረቶችን ጽፏል። እነዚህንም ተረቶች በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ርዕስ አንቀጽ ውስጥ አስነብቦናል።ይህም የእሱ መለያ ነበር።
📍ወግ አዋቂው ነቢይ መኮንን
ነቢይ መኮንን ሲጽፍ ብቻ ሳይሆን ሲናገርም ለዛ ካላቸው ወግ አዋቂ ጥቂት የጥበብ ሰዎች መካከል አንደኛው ነው። ለረጀም ሳምንታት በሸገር ሬድዮ" የቅዳሜ ጨዋታ" ዝግጅት ላይ በተደጋጋሚ በመቅረብ ብዙ ጉዳዮች ላይ ተጨዋውቷል።
📍ነቢይ በተውኔት ውስጥ
ነቢይ መኮንን "ናትናኤል ጠቢቡ" እና " ጁሊየስ ቄሳር" የተሰኙ ተውኔቶችን ተርጉሟል።በቀድሞ ጊዜም በአንዳንድ ተውኔቶች ላይ በተዋናይነት እንደተሳተፈም ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
📍የቴሌቪዥን ድራማ ጸሐፊው ነቢይ መኮንን
ነቢይ መኮንን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ይተላለፍ በነበረው "ባለጉዳይ" የተሰኘ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ላይ በድርሰት እና ተዋይነት ሰርቷል።
📍የሙዚቃ ግጥም ጸሐፊው ነቢይ መኮንን
ነቢይ መኮንን በሙዚቃ ግጥም የተሳተፈባቸው የሙዚቃ ስራዎችም አሉ።ከእነዚህም መካከል በኤችአይቪ ወረርሽኝ ጊዜ የተሰራው "ማለባበስ ይቅር" በተሰኘው ሙዚቃ ላይ በግጥም ተሳትፏል።
📍የነቢይ ህልፈት
ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ባደረበት ህመም ህክምና ሲከታተል ቆይቶ፣ ድንገት ያረፈው ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ረፋዱ ላይ ነው።
1948 እንደተወለደ የሚነገረው ደራሲ እና ወግ አዋቂው ነቢይ ህይወቱ ያለፈው በተወለደ በ68 ዓመቱ ነው።
የሶስት ሴት ልጆች አባት የሆነው የነቢይ መኮንን የቀብር ስርዓት፤ ባለቤቱ እና ልጁ ከውጭ ሀገር ከመጡ በኋላ እንደሚፈፀም ተነግሯል።
(መረጃ አሰባሳቢ: ናቲ ማናዬ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ)
ለተጨማሪው: @EventAddis1
@EventAddis1
ታላቁ የጥበብ ሰው ነቢይ መኮንን ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 26 2016 ዓ.ም ማረፉ ተሰምቷል።ስለዚህ ግዙፍ ኢትዮጵያዊ የጥበብ ሰው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘውን መረጃ እንደሚከተለው ያቀርባል።
📍ነበይ መኮንን
አንጋፋ ጋዜጠኛ፣ ደራሲ ፣ ገጣሚ እና ትርጓሜ ነው።
📍ጋዜጠኛው ነቢይ መኮንን
-አንጋፋው ጋዜጠኛ ነቢይ መኮንን ለረጅም ዓመታት የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል።
-ነቢይ መኮንን ከአዲስ አድማስ መሥራቾች አንዱ ሲሆን በዋና አዘጋጅነት ጋዜጣዋን በመምራት ተወዳጅ ካደረጓት በቀዳሚነት ስሙ ይጠቀሳል።
📍ገጣሚው ነቢይ መኮንን
ገጣሚ ነቢይ መኮንን፤ “ስውር ስፌት” ቁጥር አንድና ሁለት፣ የግጥም መድበሎችን ጨምሮ በርካታ የግጥም ስራዎችን በተለያዩ መድረኮች በማቅረብ ይታወቃል፡፡
📍ደራሲው ነቢይ መኮንን
“የኛ ሰው በአሜሪካ” እና "የመጨረሻው ንግግር " የተሰኙ መጻሕፍቱ ዝነኛ ስራዎቹ ናቸው።
📍ተርጓሚው ነቢይ መኮንን
በአሜሪካዊቷ ደራሲ ማርጋሬት ሚሼል ተደርሶ፤ በመላው ዓለም ከፍተኛ ተነባቢነትን ያገኘውን “Gone With The Wind” የተሰኘውን ረጅም ልብ ወለድ መጽሐፍ በቁርጭራጭ የሲጋራ ወረቀቶች ላይ ተርጉሞ“ነገም ሌላ ቀን ነው” በሚል ርዕስ አስነብቧል፡፡
📍ተረት ጸሐፊው ነቢይ መኮንን
ነቢይ መኮንን ወደ 700 ገደማ ተረቶችን ጽፏል። እነዚህንም ተረቶች በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ርዕስ አንቀጽ ውስጥ አስነብቦናል።ይህም የእሱ መለያ ነበር።
📍ወግ አዋቂው ነቢይ መኮንን
ነቢይ መኮንን ሲጽፍ ብቻ ሳይሆን ሲናገርም ለዛ ካላቸው ወግ አዋቂ ጥቂት የጥበብ ሰዎች መካከል አንደኛው ነው። ለረጀም ሳምንታት በሸገር ሬድዮ" የቅዳሜ ጨዋታ" ዝግጅት ላይ በተደጋጋሚ በመቅረብ ብዙ ጉዳዮች ላይ ተጨዋውቷል።
📍ነቢይ በተውኔት ውስጥ
ነቢይ መኮንን "ናትናኤል ጠቢቡ" እና " ጁሊየስ ቄሳር" የተሰኙ ተውኔቶችን ተርጉሟል።በቀድሞ ጊዜም በአንዳንድ ተውኔቶች ላይ በተዋናይነት እንደተሳተፈም ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
📍የቴሌቪዥን ድራማ ጸሐፊው ነቢይ መኮንን
ነቢይ መኮንን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ይተላለፍ በነበረው "ባለጉዳይ" የተሰኘ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ላይ በድርሰት እና ተዋይነት ሰርቷል።
📍የሙዚቃ ግጥም ጸሐፊው ነቢይ መኮንን
ነቢይ መኮንን በሙዚቃ ግጥም የተሳተፈባቸው የሙዚቃ ስራዎችም አሉ።ከእነዚህም መካከል በኤችአይቪ ወረርሽኝ ጊዜ የተሰራው "ማለባበስ ይቅር" በተሰኘው ሙዚቃ ላይ በግጥም ተሳትፏል።
📍የነቢይ ህልፈት
ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ባደረበት ህመም ህክምና ሲከታተል ቆይቶ፣ ድንገት ያረፈው ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ረፋዱ ላይ ነው።
1948 እንደተወለደ የሚነገረው ደራሲ እና ወግ አዋቂው ነቢይ ህይወቱ ያለፈው በተወለደ በ68 ዓመቱ ነው።
የሶስት ሴት ልጆች አባት የሆነው የነቢይ መኮንን የቀብር ስርዓት፤ ባለቤቱ እና ልጁ ከውጭ ሀገር ከመጡ በኋላ እንደሚፈፀም ተነግሯል።
(መረጃ አሰባሳቢ: ናቲ ማናዬ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ)
ለተጨማሪው: @EventAddis1
@EventAddis1
Event Addis Media
ስለ ነቢይ መኮንን አንዳንድ መረጃዎች ታላቁ የጥበብ ሰው ነቢይ መኮንን ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 26 2016 ዓ.ም ማረፉ ተሰምቷል።ስለዚህ ግዙፍ ኢትዮጵያዊ የጥበብ ሰው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘውን መረጃ እንደሚከተለው ያቀርባል። 📍ነበይ መኮንን አንጋፋ ጋዜጠኛ፣ ደራሲ ፣ ገጣሚ እና ትርጓሜ ነው። 📍ጋዜጠኛው ነቢይ መኮንን -አንጋፋው ጋዜጠኛ ነቢይ መኮንን ለረጅም ዓመታት የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ…
የነቢይ መኮንን የቀብር ሥነሥርዓት ነገ ይፈፀማል
ታላቁ ብዕረኛ ነቢይ መኮንን ዛሬ ማለዳ ለዘላለም ከማሸለቡ አስቀድሞ ይህንን አለ፦ "በምወዳት ከተማዬ ናዝሬት፣ ከምወዳት እናቴ ማረፊያ ቅድስት ማርያም ቤ/ክርስቲያን ቅበሩኝ"
ቤተሰቦቹ እንደገለጹልኝ ከኾነ የቀብር ስነሥርዓቱ ነገ ሐሙስ ሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ/ም ከቀኑ በ9 ሰዓት አዳማ /ናዝሬት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ይፈጸማል።
ከዚያ አስቀድሞ አንጋፋ የኪነጥበብ ሙያ አጋሮቹ ወዳጅ ዘመዶቹ እና አድናቂዎቹ በተገኙበት በታላቁ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ከጠዋት 3፣30 ሰዓት ጀምሮ እስከ 5፣00 ሰዓት ድረስ የሽኝት መርሐ ግብር ይከናወናል።
መላው የሚዲያ ማሕበረሰብ መረጃውን እንዲያዳርስላቸው እንዲሁም የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በመገኘት የሽኝት ሥነስርዓቱን እንዲታደሙ ጥሪ አቅርበዋል።
📍መረጃው የያሬድ ሹመቴ ነው።
ለተጨማሪው: @EventAddis1
@EventAddis1
ታላቁ ብዕረኛ ነቢይ መኮንን ዛሬ ማለዳ ለዘላለም ከማሸለቡ አስቀድሞ ይህንን አለ፦ "በምወዳት ከተማዬ ናዝሬት፣ ከምወዳት እናቴ ማረፊያ ቅድስት ማርያም ቤ/ክርስቲያን ቅበሩኝ"
ቤተሰቦቹ እንደገለጹልኝ ከኾነ የቀብር ስነሥርዓቱ ነገ ሐሙስ ሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ/ም ከቀኑ በ9 ሰዓት አዳማ /ናዝሬት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ይፈጸማል።
ከዚያ አስቀድሞ አንጋፋ የኪነጥበብ ሙያ አጋሮቹ ወዳጅ ዘመዶቹ እና አድናቂዎቹ በተገኙበት በታላቁ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ከጠዋት 3፣30 ሰዓት ጀምሮ እስከ 5፣00 ሰዓት ድረስ የሽኝት መርሐ ግብር ይከናወናል።
መላው የሚዲያ ማሕበረሰብ መረጃውን እንዲያዳርስላቸው እንዲሁም የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በመገኘት የሽኝት ሥነስርዓቱን እንዲታደሙ ጥሪ አቅርበዋል።
📍መረጃው የያሬድ ሹመቴ ነው።
ለተጨማሪው: @EventAddis1
@EventAddis1
Event Addis Media
Photo
የሐሙስ መረጃዎች
የሳምንቱን ኪናዊ መረጃዎችን እነሆ:
📍መረጃውን ሲጠቀሙ ምንጭ ይጠቀሱ!
1.የአንጋፋው ጋዜጠኛ ፣ገጣሚ፣ ደራሲና ተርጓሚ ነቢይ መኮንን የሽኝትና ቀብር ሥነሥርዓት ዛሬ ሰኔ 27 2016 ዓ.ም ይፈፀማል።የሽኝት መርሐግብሩ ከጠዋቱ 3:30 እስከ 5:00 በብሔራዊ ቴአትር የሚካሄድ ሲሆን ከቀኑ 9:00 ላይ በአዳማ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የቀብር ሥነሥርዓቱ ይፈፀማል ተብሏል።
2.ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ በ"USA TOUR" በአሜሪካ ከዛሬ ጀምሮ የሙዚቃ ስራውን ማቅረብ ይጀምራል ተብሏል። ሙዚቀኛው ዛሬ በአትላንታ የሙዚቃ ስራውን ማቅረብ የሚጀምር ሲሆን በማስከተል በስድስት የአሜሪካ ግዛቶች የሙዚቃ ኮንሰርቱን እንደሚያቀርብ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል። ይህም የሙዚቃ ዝግጅት ጉዞው የሮፍናን ኑሪ ዘጠኛ(ኖር እና ሐራንቤ) አልበም ከተለቀቀ በኃላ የመጀመሪያው ነው።
3.የድምጻዊት ሰላማዊት ዮሐንስ "ሰንቢደ" የተሰኘ የትግርኛ ሙዚቃ ነገ በናሆም ሪከርድስ በኩል ለአድማጮች ይደርሳል።በሙዚቃው ላይ በግጥም ውቅያኖስ ጉዕሽ በዜማና ሙዚቃ ቅንብር በረኸት ወልዱ ተሳትፈዋል።ድምጻዊት ሰላማዊት ዮሐንስ ከዚህ ቀደም በዩቲዩብ ከፍተኛ ተመልካች ያገኘችባቸውን "ዞማዋ" "ሰናይ " "የብለኒሎ"ን ጨምሮ በርካታ ነጠላ ሙዚቃዎችን ለአድማጮች አድርሳለች።
4."የአርክውድ አፍሪካ የፊልም ገበያ እና ሽልማት 2017 ቅደመ ዝግጅት" የተሰኘ ጉባኤ ሰኔ 28 እና 29 2016 ዓ.ም ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ አድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ውስጥ ይካሄዳል። ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ የፊልም ባለሞያዎች በዚህ ጉባኤ ላይ እንደሚሳተፉ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
5.ከደራስያን ጋር የመጨዋወት እና መጽሐፍ የማስፈረም ልዩ ሥነ-ሥርዓት የፊታችን ቅዳሜ በዋልያ መጻሕፍት ይካሄዳል። በዚህ ሳምንት በደራሲ አለማየሁ ገላጋይ "ማዕበል ጠሪ ወፍ" በተሰኘው መጽሐፍ ላይ ውይይት ይካሄዳል ።በመጽሐፉ ላይ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ እና ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ዳሰሳ ያቀርባሉ ተብሏል። ይህ ውይይት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 29 2016 ዓ. ም ከሰዓት 10:00 እስከ 12:30 ድረስ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ ይካሄዳል።
6.የገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ "የጊዜ ሰሌዳ" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 1 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ልዩ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል። "የጊዜ ሠሌዳ" መጽሐፍ በ103 ገፆች ተቀንብቡ በ250 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል። ገጣሚዋ ከዚህ ቀደም "የቃል ሠሌዳ" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል።
7. በኔትፍሊክስ በኩል ለተመልካቾች ሊቀረብ ይችላል የተባለውና በደራሲ እና ዳይሬክተር ፍፁም ካሣሁን የተሰራው "ጥቁር አደይ" ፊልም የፊታችን ሐምሌ 10 2016 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል ተብሏል።በፊልሙ ላይ ሚኪ ተስፋዬ ፤ ካሣሁን ፍስሐ፣ማንዴላ፤ ናታን ጌታቸው፤ ነቢዩ እንድሪስ፣ ኤደን አይሸሹምን ጨምሮ ከ186 በላይ ተዋናያን እንደተሳተፉበት አዘጋጆቹ ለኤቨንት አዲስ ድረገፅ ተናግረዋል።
8."እሳት ወይ አበባ" ተውኔት ነገ ወደ መድረክ ይመለሳል። በሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ግጥሞች ላይ የተመሰረተው "እሳት ወይ አበባ" ግጥማዊ ዳንስ ተውኔት በብሔራዊ ቴአትር ከነገ ሰኔ 28 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ መድረክ እንደሚመለስ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከአዘጋጆቹ ያገኘው መረጀ ያመለክታል።
9.በዓለምአቀፍ ደረጃ ስመ ገናና የሆነውን "MosFilm" ስቱዲዮ 100ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ የሩሲያ ሳይንስና ባህል ማዕከል ከአላቲኖስ ኢትዮጵያዊ ፊልም ሰሪዎች ማህበር ጋር በመተባበር ዘመን አይሽሬ የMosFilms ፊልሞችን ከዛሬ ሐሙስ ሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እና 12:00፣ቅዳሜ ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እስከ 12:00 እንዲሁም እሁድ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እስከ 12:00 ከአንድሬ ታርኮቭስኪ እስከ ኦስካር አሸናፊ ፊልሞች በነፃ ለታዳሚያን ያቀርባል። ይህም የፊልም ሳምንት ፒያሳ በሚገኘዉ የፑሽኪን ሲኒማ አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።
10.በግራፊክስ ዲዛይነር ፋኑኤል ልዑል የተዘጋጁ የዲጂታል ጥበብ ስራዎች የሚቀርቡበት "የተሰወረውን መሻት" የተሰኘ የዲጂታል ጥበብ አውደርዕይ ባሳለፍነው ሰኞ ሰኔ 24 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ካዛንቺስ በሚገኘው ፈንድቃ የባህል ማዕከል ውስጥ ተከፍቷል።ይህ የዲጂታል ጥበብ አውደርዕይ እስከ ሐምሌ 8 2016 ዓ.ም ድረስ በእይታ ላይ ይቆያል ተብሏል።የግራፊክስ ዲዛይነሩ ፋኑኤል ልዑል ከዓመታት በፊት ለአድማጮች የደረሰው የሮፍናን ኑሪ"ስድስት" አልበም ሽፋን(ከቨር) ዲዛይኑን መስራቱ ይታወሳል።
አዘጋጅ: ናቲ ማናዬ
ቀን: ሰኔ 27 2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
በድረገጻችን በተሻለ አቀራረብ ያንብቡ:
https://eventaddis.com
ቴሌግራም: @EventAddis1
የሳምንቱን ኪናዊ መረጃዎችን እነሆ:
📍መረጃውን ሲጠቀሙ ምንጭ ይጠቀሱ!
1.የአንጋፋው ጋዜጠኛ ፣ገጣሚ፣ ደራሲና ተርጓሚ ነቢይ መኮንን የሽኝትና ቀብር ሥነሥርዓት ዛሬ ሰኔ 27 2016 ዓ.ም ይፈፀማል።የሽኝት መርሐግብሩ ከጠዋቱ 3:30 እስከ 5:00 በብሔራዊ ቴአትር የሚካሄድ ሲሆን ከቀኑ 9:00 ላይ በአዳማ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የቀብር ሥነሥርዓቱ ይፈፀማል ተብሏል።
2.ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ በ"USA TOUR" በአሜሪካ ከዛሬ ጀምሮ የሙዚቃ ስራውን ማቅረብ ይጀምራል ተብሏል። ሙዚቀኛው ዛሬ በአትላንታ የሙዚቃ ስራውን ማቅረብ የሚጀምር ሲሆን በማስከተል በስድስት የአሜሪካ ግዛቶች የሙዚቃ ኮንሰርቱን እንደሚያቀርብ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል። ይህም የሙዚቃ ዝግጅት ጉዞው የሮፍናን ኑሪ ዘጠኛ(ኖር እና ሐራንቤ) አልበም ከተለቀቀ በኃላ የመጀመሪያው ነው።
3.የድምጻዊት ሰላማዊት ዮሐንስ "ሰንቢደ" የተሰኘ የትግርኛ ሙዚቃ ነገ በናሆም ሪከርድስ በኩል ለአድማጮች ይደርሳል።በሙዚቃው ላይ በግጥም ውቅያኖስ ጉዕሽ በዜማና ሙዚቃ ቅንብር በረኸት ወልዱ ተሳትፈዋል።ድምጻዊት ሰላማዊት ዮሐንስ ከዚህ ቀደም በዩቲዩብ ከፍተኛ ተመልካች ያገኘችባቸውን "ዞማዋ" "ሰናይ " "የብለኒሎ"ን ጨምሮ በርካታ ነጠላ ሙዚቃዎችን ለአድማጮች አድርሳለች።
4."የአርክውድ አፍሪካ የፊልም ገበያ እና ሽልማት 2017 ቅደመ ዝግጅት" የተሰኘ ጉባኤ ሰኔ 28 እና 29 2016 ዓ.ም ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ አድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ውስጥ ይካሄዳል። ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ የፊልም ባለሞያዎች በዚህ ጉባኤ ላይ እንደሚሳተፉ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
5.ከደራስያን ጋር የመጨዋወት እና መጽሐፍ የማስፈረም ልዩ ሥነ-ሥርዓት የፊታችን ቅዳሜ በዋልያ መጻሕፍት ይካሄዳል። በዚህ ሳምንት በደራሲ አለማየሁ ገላጋይ "ማዕበል ጠሪ ወፍ" በተሰኘው መጽሐፍ ላይ ውይይት ይካሄዳል ።በመጽሐፉ ላይ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ እና ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ዳሰሳ ያቀርባሉ ተብሏል። ይህ ውይይት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 29 2016 ዓ. ም ከሰዓት 10:00 እስከ 12:30 ድረስ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ ይካሄዳል።
6.የገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ "የጊዜ ሰሌዳ" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 1 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ልዩ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል። "የጊዜ ሠሌዳ" መጽሐፍ በ103 ገፆች ተቀንብቡ በ250 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል። ገጣሚዋ ከዚህ ቀደም "የቃል ሠሌዳ" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል።
7. በኔትፍሊክስ በኩል ለተመልካቾች ሊቀረብ ይችላል የተባለውና በደራሲ እና ዳይሬክተር ፍፁም ካሣሁን የተሰራው "ጥቁር አደይ" ፊልም የፊታችን ሐምሌ 10 2016 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል ተብሏል።በፊልሙ ላይ ሚኪ ተስፋዬ ፤ ካሣሁን ፍስሐ፣ማንዴላ፤ ናታን ጌታቸው፤ ነቢዩ እንድሪስ፣ ኤደን አይሸሹምን ጨምሮ ከ186 በላይ ተዋናያን እንደተሳተፉበት አዘጋጆቹ ለኤቨንት አዲስ ድረገፅ ተናግረዋል።
8."እሳት ወይ አበባ" ተውኔት ነገ ወደ መድረክ ይመለሳል። በሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ግጥሞች ላይ የተመሰረተው "እሳት ወይ አበባ" ግጥማዊ ዳንስ ተውኔት በብሔራዊ ቴአትር ከነገ ሰኔ 28 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ መድረክ እንደሚመለስ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከአዘጋጆቹ ያገኘው መረጀ ያመለክታል።
9.በዓለምአቀፍ ደረጃ ስመ ገናና የሆነውን "MosFilm" ስቱዲዮ 100ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ የሩሲያ ሳይንስና ባህል ማዕከል ከአላቲኖስ ኢትዮጵያዊ ፊልም ሰሪዎች ማህበር ጋር በመተባበር ዘመን አይሽሬ የMosFilms ፊልሞችን ከዛሬ ሐሙስ ሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እና 12:00፣ቅዳሜ ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እስከ 12:00 እንዲሁም እሁድ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 እስከ 12:00 ከአንድሬ ታርኮቭስኪ እስከ ኦስካር አሸናፊ ፊልሞች በነፃ ለታዳሚያን ያቀርባል። ይህም የፊልም ሳምንት ፒያሳ በሚገኘዉ የፑሽኪን ሲኒማ አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።
10.በግራፊክስ ዲዛይነር ፋኑኤል ልዑል የተዘጋጁ የዲጂታል ጥበብ ስራዎች የሚቀርቡበት "የተሰወረውን መሻት" የተሰኘ የዲጂታል ጥበብ አውደርዕይ ባሳለፍነው ሰኞ ሰኔ 24 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ካዛንቺስ በሚገኘው ፈንድቃ የባህል ማዕከል ውስጥ ተከፍቷል።ይህ የዲጂታል ጥበብ አውደርዕይ እስከ ሐምሌ 8 2016 ዓ.ም ድረስ በእይታ ላይ ይቆያል ተብሏል።የግራፊክስ ዲዛይነሩ ፋኑኤል ልዑል ከዓመታት በፊት ለአድማጮች የደረሰው የሮፍናን ኑሪ"ስድስት" አልበም ሽፋን(ከቨር) ዲዛይኑን መስራቱ ይታወሳል።
አዘጋጅ: ናቲ ማናዬ
ቀን: ሰኔ 27 2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
በድረገጻችን በተሻለ አቀራረብ ያንብቡ:
https://eventaddis.com
ቴሌግራም: @EventAddis1
የአንጋፋው ከያኒ ነቢይ መኮንን ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ
አንጋፋው የኪነ ጥበብ ባለሞያ፣ ገጣሚ፣ ደራሲ፣ ፀሃፊና ተርጓሚ ነብይ መኮንን ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ትላንት ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ማለፉ መገለጹ ይታወሳል፡፡
በዛሬው ሰኔ 27 2016 ዓ.ም በብሄራዊ ቴአትር ቤት በሙያ ጓደኞቹ የአሸኛኘት ፕሮግራም የተከናወነለት ሲሆን፣ በመቀጠልም በተወለደበት እና ባደገበት ናዝሬት ከተማ ሥርዓተ ቀብሩ ተፈጽሟል፡፡
ለተጨማሪው: @EventAddis1
@EventAddis1
አንጋፋው የኪነ ጥበብ ባለሞያ፣ ገጣሚ፣ ደራሲ፣ ፀሃፊና ተርጓሚ ነብይ መኮንን ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ትላንት ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ማለፉ መገለጹ ይታወሳል፡፡
በዛሬው ሰኔ 27 2016 ዓ.ም በብሄራዊ ቴአትር ቤት በሙያ ጓደኞቹ የአሸኛኘት ፕሮግራም የተከናወነለት ሲሆን፣ በመቀጠልም በተወለደበት እና ባደገበት ናዝሬት ከተማ ሥርዓተ ቀብሩ ተፈጽሟል፡፡
ለተጨማሪው: @EventAddis1
@EventAddis1
የቅድስት ይልማ "ጀስቲሺያ" ፊልም ለእይታ ሊበቃ ነው
የዳይሬክተር ቅድስት ይልማ "ጀስቲሺያ" የተሰኘ ፊልም ከሐምሌ 5 2016 ዓ.ም ጀምሮ በዓለም ሲኒማ ለእይታ እንደሚበቃ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
የ"ጀስቲሺያ" ፊልም ዳይሬክተር ቅድስት ይልማ ስትሆን አዜብ ወርቁ እና ቅድስት ይልማ በፊልም ጽሑፍ ተሳትፈዋል።
ህሊና ሲሳይ ፣እድለወርቅ ጣሰው ፣ ድርብወርቅ ሰይፉ ፣ቢታኒያ መስፍን ፣ኤደን ግርማና ሌሎችሞ በተዋናይነት ተሳትፈዋል።
"ጀስቲሺያ" የቤት ሰራተኞን የተመለከተ የህግ ማዕቀፍ እንዲወጣ ግንዛቤ መፍጠርን ዓላማ ይዞ የተሰራ ፊልም እንደሆነ ተሰምቷል።
ለተጨማሪው: @EventAddis1
@EventAddis1
የዳይሬክተር ቅድስት ይልማ "ጀስቲሺያ" የተሰኘ ፊልም ከሐምሌ 5 2016 ዓ.ም ጀምሮ በዓለም ሲኒማ ለእይታ እንደሚበቃ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
የ"ጀስቲሺያ" ፊልም ዳይሬክተር ቅድስት ይልማ ስትሆን አዜብ ወርቁ እና ቅድስት ይልማ በፊልም ጽሑፍ ተሳትፈዋል።
ህሊና ሲሳይ ፣እድለወርቅ ጣሰው ፣ ድርብወርቅ ሰይፉ ፣ቢታኒያ መስፍን ፣ኤደን ግርማና ሌሎችሞ በተዋናይነት ተሳትፈዋል።
"ጀስቲሺያ" የቤት ሰራተኞን የተመለከተ የህግ ማዕቀፍ እንዲወጣ ግንዛቤ መፍጠርን ዓላማ ይዞ የተሰራ ፊልም እንደሆነ ተሰምቷል።
ለተጨማሪው: @EventAddis1
@EventAddis1
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ኦንላየን ሲኒማ ተመረቀ
በሀገራችን የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማበልፀግ የሚታወቀው ኢግልላየን ቴክኖሎጂ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር "ቴሌ ቲቪ" የተሰኘ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የኦንላይን ሲኒማ አስመርቋል።
"ቴሌ ቲቪ" በኢትዮጵያ ያለውን ፊልም የመከራየት ልምድ በቴክኖሎጂ በማዘመን ፊልሞችን ለተገደቡ ቀናት በመከራየት ማየት የሚያስችል መተግበሪያ ነው።
መተግበሪያውም ከቅርብ ግዜ ወዲህ በፊልሙ ኢንዱስትሪ መሰናክል ሆኖ የቆየውን የፊልም ስርቆት የሚያስቀር መሆኑን የኤግላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ መስራች እና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት በእርሱፍቃድ ጌታቸው ገልጸዋል።
ተመልካቾች ከዛሬ ጀምረው ፊልሞችን መከራየት የሚችሉ እንደሆነ እና ክፍያም ለሀገር ውስጥ ደንበኞች በቴሌ ብር እንዲሁም በውጪ ሀገር ለሚኖሩ የአማርኛ ፊልም ተመልካቾች በቪዛ፣ ማስተር ካርድ እና አሜሪካን ኤክስፕረስ በመጠቀም ይችላሉ ተብሏል።
📍መረጃው የኤንቢሲ ቴሌቪዥን ነው።
ለተጨማሪው: @EventAddis1
በሀገራችን የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማበልፀግ የሚታወቀው ኢግልላየን ቴክኖሎጂ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር "ቴሌ ቲቪ" የተሰኘ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የኦንላይን ሲኒማ አስመርቋል።
"ቴሌ ቲቪ" በኢትዮጵያ ያለውን ፊልም የመከራየት ልምድ በቴክኖሎጂ በማዘመን ፊልሞችን ለተገደቡ ቀናት በመከራየት ማየት የሚያስችል መተግበሪያ ነው።
መተግበሪያውም ከቅርብ ግዜ ወዲህ በፊልሙ ኢንዱስትሪ መሰናክል ሆኖ የቆየውን የፊልም ስርቆት የሚያስቀር መሆኑን የኤግላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ መስራች እና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት በእርሱፍቃድ ጌታቸው ገልጸዋል።
ተመልካቾች ከዛሬ ጀምረው ፊልሞችን መከራየት የሚችሉ እንደሆነ እና ክፍያም ለሀገር ውስጥ ደንበኞች በቴሌ ብር እንዲሁም በውጪ ሀገር ለሚኖሩ የአማርኛ ፊልም ተመልካቾች በቪዛ፣ ማስተር ካርድ እና አሜሪካን ኤክስፕረስ በመጠቀም ይችላሉ ተብሏል።
📍መረጃው የኤንቢሲ ቴሌቪዥን ነው።
ለተጨማሪው: @EventAddis1
የሜንታል ሄልዝ አዲስ መርሃግብር ነገ ይካሄዳል
ወርሃዊው የሜንታል ሄልዝ አዲስ መርሃግብር ነገ ቅዳሜ ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓም አትላስ አካባቢ በሚገኘው በአዶር አዲስ ሆቴል ከቀኑ 10፡00 ጀምሮ ይካሄዳል።
የዚህ ወር ርዕስም፡- “A Journey to Deal with Secondary Trauma of Health Professionals and Gender-Based Violence Survivors” የሚል ሲሆን የዚህ ወር እንግዳ ዶ/ር ሰብለ ሃይሉ ናቸው፡፡
ለመታደም ይህን መስፈንጠሪያ ይጫኑና ይመዝገቡ፡፡
https://forms.gle/gMnmRBBSfhR7YyYB6
የማስታወሻ መልዕክት እና የቦታውን አቅጣጫ ምልክት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከተሉ https://news.1rj.ru/str/mhaddisababa
ለተጨማሪው: @EventAddis1
ወርሃዊው የሜንታል ሄልዝ አዲስ መርሃግብር ነገ ቅዳሜ ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓም አትላስ አካባቢ በሚገኘው በአዶር አዲስ ሆቴል ከቀኑ 10፡00 ጀምሮ ይካሄዳል።
የዚህ ወር ርዕስም፡- “A Journey to Deal with Secondary Trauma of Health Professionals and Gender-Based Violence Survivors” የሚል ሲሆን የዚህ ወር እንግዳ ዶ/ር ሰብለ ሃይሉ ናቸው፡፡
ለመታደም ይህን መስፈንጠሪያ ይጫኑና ይመዝገቡ፡፡
https://forms.gle/gMnmRBBSfhR7YyYB6
የማስታወሻ መልዕክት እና የቦታውን አቅጣጫ ምልክት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይከተሉ https://news.1rj.ru/str/mhaddisababa
ለተጨማሪው: @EventAddis1
የመጻሕፍት አውደርዕይ በኢግዚብሽን ማዕከል
የአዲስ አበባ ከተማ ባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 9ኛ ዙር የንባብ ፌስቲቫል “ንባብ ለትውልድ ግንባታ!” በሚል መሪ ቃል ከዛሬ ሰኔ 28 እስከ ሰኔ 30 2016 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ይካሄዳል፡፡
ቴሌግራም: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ድረገፅ: https://eventaddis.com
የአዲስ አበባ ከተማ ባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 9ኛ ዙር የንባብ ፌስቲቫል “ንባብ ለትውልድ ግንባታ!” በሚል መሪ ቃል ከዛሬ ሰኔ 28 እስከ ሰኔ 30 2016 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ይካሄዳል፡፡
ቴሌግራም: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ድረገፅ: https://eventaddis.com
"ሚውዚኮሎጂ" የቴሌቪዥን ዝግጅት በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ(Addis TV) መቅረብ ሊጀምር ነው።
በሄኖክ መሓሪ (መሓሪ ብራዘርስ) እየተዘጋጅ የሚቀረበው "ሚውዚኮሎጂ" የሙዚቃ እና ሙዚቀኞች የቴሌቪዥን ዝግጅት በቅርቡ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ( Addis TV) መቅረብ እንደሚጀመር ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከአዘጋጁ ሄኖክ መሓሪ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በ ቃና እና አቦል ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለዓመታት ሲቀረብ የቆየው "ሚውዚኮሎጂ" የቴሌቪዥን ዝግጅት ዘወትር እሁድ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (Addis TV) እና በዩቲዩብ አማራጮች ለተመልካቾች ይቀርባል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በሄኖክ መሓሪ (መሓሪ ብራዘርስ) እየተዘጋጅ የሚቀረበው "ሚውዚኮሎጂ" የሙዚቃ እና ሙዚቀኞች የቴሌቪዥን ዝግጅት በቅርቡ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ( Addis TV) መቅረብ እንደሚጀመር ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከአዘጋጁ ሄኖክ መሓሪ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በ ቃና እና አቦል ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለዓመታት ሲቀረብ የቆየው "ሚውዚኮሎጂ" የቴሌቪዥን ዝግጅት ዘወትር እሁድ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (Addis TV) እና በዩቲዩብ አማራጮች ለተመልካቾች ይቀርባል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሮፍናን እና ክሪስ ብራውን ተጣምሩ !
ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ እና አሜሪካዊው ድምጻዊ ክሪስ ብራውን በአንድ መድረክ ዝግጅታቸውን ሊያቀርቡ ነው።
ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ ዓለምአቀፍ ድምጻዊ ክሪስ ብራውን የሙዚቃ ዝግጅታቸውን ነገ ሰኔ 29 2016 ዓ.ም በአሜሪካ አትላንታ በአንድ መድረክ ሊቀርቡ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
አሜሪካዊው ክሪስ ብራውን ራፐር ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ ፣ ተዋናይ እና ተወዛዋዥ ሲሆን በ "አር ኤንድ ቢ" የሙዚቃ ስልት በመላው ዓለም ዝነኛ ከሆኑ ሙዚቀኞች አንደኛው ነው።
ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ በ"USA TOUR" በአሜሪካ ከትላንት ጀምሮ የሙዚቃ ስራውን ማቅረብ ጀምሯል።
ይህም የሙዚቃ ዝግጅት ጉዞው የሮፍናን ኑሪ ዘጠኛ(ኖር እና ሐራንቤ) አልበም ከተለቀቀ በኃላ የመጀመሪያው ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ እና አሜሪካዊው ድምጻዊ ክሪስ ብራውን በአንድ መድረክ ዝግጅታቸውን ሊያቀርቡ ነው።
ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ ዓለምአቀፍ ድምጻዊ ክሪስ ብራውን የሙዚቃ ዝግጅታቸውን ነገ ሰኔ 29 2016 ዓ.ም በአሜሪካ አትላንታ በአንድ መድረክ ሊቀርቡ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
አሜሪካዊው ክሪስ ብራውን ራፐር ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ ፣ ተዋናይ እና ተወዛዋዥ ሲሆን በ "አር ኤንድ ቢ" የሙዚቃ ስልት በመላው ዓለም ዝነኛ ከሆኑ ሙዚቀኞች አንደኛው ነው።
ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ በ"USA TOUR" በአሜሪካ ከትላንት ጀምሮ የሙዚቃ ስራውን ማቅረብ ጀምሯል።
ይህም የሙዚቃ ዝግጅት ጉዞው የሮፍናን ኑሪ ዘጠኛ(ኖር እና ሐራንቤ) አልበም ከተለቀቀ በኃላ የመጀመሪያው ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ደራሲ ኃይለጊዮርጊስ ማሞ እና ልጁ ተመረቁ
"ጥበብ ከጲላጦስ" ተከታታይ መጻህፍትን ጨምሮ በልዩ ልዩ መጽሔቶች ጸሐፊነቱ የምናውቀው ደራሲ ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር) ከመጀመሪያ ሴት ልጁ ጋር በመሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተመርቀዋል።
ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ክፍል ለመጀመሪያ ጊዜ በፒኤችዲ ዲግሪ ካስመረቃቸው ሶስት ምሩቃን መካከል አንዱ ሆኗል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"ጥበብ ከጲላጦስ" ተከታታይ መጻህፍትን ጨምሮ በልዩ ልዩ መጽሔቶች ጸሐፊነቱ የምናውቀው ደራሲ ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር) ከመጀመሪያ ሴት ልጁ ጋር በመሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተመርቀዋል።
ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ክፍል ለመጀመሪያ ጊዜ በፒኤችዲ ዲግሪ ካስመረቃቸው ሶስት ምሩቃን መካከል አንዱ ሆኗል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ አጠገብ ስለሚገኘው"የይሁዳ አንበሳ" አጭር መረጃን እነሆ !
በምስሉ ላይ የሚገኘውን መረጃ ያንብቡ !
📍ምንጭ: መዲና ዲጂታል መጽሔት
ማስታወሻ: መዲና ዲጂታል መጽሔት ቅጽ አንድ ቁጥር 4 ዲጂታል መጽሔት በነፃ ለአንባቢያን ቀርባለች። የሚከተለውን ሊንክ በመጠቀም መዲና ዲጂታል መጽሔትን ማንበብ ትችላላችሁ።
https://news.1rj.ru/str/Medinamagazine
በተጨማሪም በፌስቡክ እና ኢንስታግራም ቤተሰብ ልትሆኑ ትችላላችሁ።
https://www.facebook.com/profile.php?id=61556884335163&mibextid=ZbWKwL
https://www.instagram.com/medinadigitalmegazine?igsh=ejZqbjN3OXF0dHJj
በምስሉ ላይ የሚገኘውን መረጃ ያንብቡ !
📍ምንጭ: መዲና ዲጂታል መጽሔት
ማስታወሻ: መዲና ዲጂታል መጽሔት ቅጽ አንድ ቁጥር 4 ዲጂታል መጽሔት በነፃ ለአንባቢያን ቀርባለች። የሚከተለውን ሊንክ በመጠቀም መዲና ዲጂታል መጽሔትን ማንበብ ትችላላችሁ።
https://news.1rj.ru/str/Medinamagazine
በተጨማሪም በፌስቡክ እና ኢንስታግራም ቤተሰብ ልትሆኑ ትችላላችሁ።
https://www.facebook.com/profile.php?id=61556884335163&mibextid=ZbWKwL
https://www.instagram.com/medinadigitalmegazine?igsh=ejZqbjN3OXF0dHJj
"የጊዜ ሰሌዳ" መጽሐፍ ዛሬ ይመረቃል
የገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ "የጊዜ ሰሌዳ" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 1 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ልዩ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል።
በዕለቱም ጸሐፌተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ ኃይለመለኮተ መዋዕለ ፣ አርቲስት አዳነች ወ/ገብርኤል፣ አርቲስት ድርብወርቅ ሰይፉ ፣ አርቲስት ፈለቀ ካሣ፣ ደራሲ የዝና ወርቁ፣ ደራሲ ሮማን ተወልደብርሃን በክብር እንግድነት ይገኛሉ።
ገጣሚያኑ ቴዎድሮስ ካሣ፣ ባንቺአየሁ አሰፋ፣ ፌቤን ፋንጮ፣ መሰረት ጌታነህና ሌሎችም የግጥም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ።
"የጊዜ ሠሌዳ" መጽሐፍ በ103 ገፆች ተቀንብቡ በ250 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
ገጣሚዋ ከዚህ ቀደም "የቃል ሠሌዳ" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ "የጊዜ ሰሌዳ" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 1 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ልዩ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል።
በዕለቱም ጸሐፌተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ ኃይለመለኮተ መዋዕለ ፣ አርቲስት አዳነች ወ/ገብርኤል፣ አርቲስት ድርብወርቅ ሰይፉ ፣ አርቲስት ፈለቀ ካሣ፣ ደራሲ የዝና ወርቁ፣ ደራሲ ሮማን ተወልደብርሃን በክብር እንግድነት ይገኛሉ።
ገጣሚያኑ ቴዎድሮስ ካሣ፣ ባንቺአየሁ አሰፋ፣ ፌቤን ፋንጮ፣ መሰረት ጌታነህና ሌሎችም የግጥም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ።
"የጊዜ ሠሌዳ" መጽሐፍ በ103 ገፆች ተቀንብቡ በ250 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
ገጣሚዋ ከዚህ ቀደም "የቃል ሠሌዳ" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የቅድስት ይልማ "ጀስቲሺያ" የተሰኘ ፊልም ከፊታችን አርብ ጀምሮ በዓለም ሲኒማ ለእይታ ይበቃል ተብሏል።
የዳይሬክተር ቅድስት ይልማ "ጀስቲሺያ" የተሰኘ ፊልም ከፊታችን አርብ ሐምሌ 5 2016 ዓ.ም ጀምሮ በዓለም ሲኒማ ለእይታ እንደሚበቃ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
የ"ጀስቲሺያ" ፊልም ዳይሬክተር ቅድስት ይልማ ስትሆን አዜብ ወርቁ እና ቅድስት ይልማ በፊልም ጽሑፍ ተሳትፈዋል።
ህሊና ሲሳይ ፣እድለወርቅ ጣሰው ፣ ድርብወርቅ ሰይፉ ፣ቢታኒያ መስፍን ፣ኤደን ግርማና ሌሎችሞ በተዋናይነት ተሳትፈዋል።
"ጀስቲሺያ" የቤት ሰራተኞን የተመለከተ የህግ ማዕቀፍ እንዲወጣ ግንዛቤ መፍጠርን ዓላማ ይዞ የተሰራ ፊልም እንደሆነ ተሰምቷል።
ለተጨማሪው: @EventAddis1
@EventAddis1
የዳይሬክተር ቅድስት ይልማ "ጀስቲሺያ" የተሰኘ ፊልም ከፊታችን አርብ ሐምሌ 5 2016 ዓ.ም ጀምሮ በዓለም ሲኒማ ለእይታ እንደሚበቃ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
የ"ጀስቲሺያ" ፊልም ዳይሬክተር ቅድስት ይልማ ስትሆን አዜብ ወርቁ እና ቅድስት ይልማ በፊልም ጽሑፍ ተሳትፈዋል።
ህሊና ሲሳይ ፣እድለወርቅ ጣሰው ፣ ድርብወርቅ ሰይፉ ፣ቢታኒያ መስፍን ፣ኤደን ግርማና ሌሎችሞ በተዋናይነት ተሳትፈዋል።
"ጀስቲሺያ" የቤት ሰራተኞን የተመለከተ የህግ ማዕቀፍ እንዲወጣ ግንዛቤ መፍጠርን ዓላማ ይዞ የተሰራ ፊልም እንደሆነ ተሰምቷል።
ለተጨማሪው: @EventAddis1
@EventAddis1
"የጊዜ ሰሌዳ" መጽሐፍ በብሔራዊ ቴአትር ቤት ተመረቀ!
የገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ "የጊዜ ሰሌዳ" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ ሐምሌ 1 2016 ዓ.ም በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ልዩ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል።
በዕለቱም ጸሐፌተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕለ ፣ አርቲስት አዳነች ወ/ገብርኤል፣ ደራሲ የዝና ወርቁ፣ወ/ሮ አስቴሮ ወ/ሚካኤል(የመንቢ እናት) እና ሌሎችም በክብር እንግድነት ተገኝተዋል።
ገጣሚያኑ ቴዎድሮስ ካሣ፣ ባንቺአየሁ አሰፋ፣ ፌቤን ፋንጮ፣ መሰረት ጌታነህ፣አስካለ ልቅና፣ ዘካሪያስ አንተነህ የግጥም ስራዎቻቸውን አቅረብዋል።
በሙዚቃው በኩል ተስፋ ፣ ቤቲ አፍሮ ፣ አብርሃም ኸይሩ እና የህብረ ዝማሬ ቡድን አባላት ነበሩ።
የውዝዋዜ ትርዒት በ"ኢትዮጵያን ባህላዊ የውዝዋዜ ቡድን" እና "የሻዳ ትርዒት " በምጣድ ፕሮዳክሽን" ቀርቧል።
"የጊዜ ሠሌዳ" መጽሐፍ በ103 ገፆች ተቀንብቡ በ250 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
ገጣሚዋ ከዚህ ቀደም "የቃል ሠሌዳ" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል።
መጽሐፉ በተለያዩ መጻሕፍት መደብሮች ይገኛል።
ፎቶ: አቤል ምህረቴ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ "የጊዜ ሰሌዳ" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ ሐምሌ 1 2016 ዓ.ም በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ልዩ ልዩ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል።
በዕለቱም ጸሐፌተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕለ ፣ አርቲስት አዳነች ወ/ገብርኤል፣ ደራሲ የዝና ወርቁ፣ወ/ሮ አስቴሮ ወ/ሚካኤል(የመንቢ እናት) እና ሌሎችም በክብር እንግድነት ተገኝተዋል።
ገጣሚያኑ ቴዎድሮስ ካሣ፣ ባንቺአየሁ አሰፋ፣ ፌቤን ፋንጮ፣ መሰረት ጌታነህ፣አስካለ ልቅና፣ ዘካሪያስ አንተነህ የግጥም ስራዎቻቸውን አቅረብዋል።
በሙዚቃው በኩል ተስፋ ፣ ቤቲ አፍሮ ፣ አብርሃም ኸይሩ እና የህብረ ዝማሬ ቡድን አባላት ነበሩ።
የውዝዋዜ ትርዒት በ"ኢትዮጵያን ባህላዊ የውዝዋዜ ቡድን" እና "የሻዳ ትርዒት " በምጣድ ፕሮዳክሽን" ቀርቧል።
"የጊዜ ሠሌዳ" መጽሐፍ በ103 ገፆች ተቀንብቡ በ250 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ቀርቧል።
ገጣሚዋ ከዚህ ቀደም "የቃል ሠሌዳ" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል።
መጽሐፉ በተለያዩ መጻሕፍት መደብሮች ይገኛል።
ፎቶ: አቤል ምህረቴ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1