FM ADDIS 97.1(ኤፍ ኤም አዲስ 97.1) – Telegram
FM ADDIS 97.1(ኤፍ ኤም አዲስ 97.1)
8.5K subscribers
1.3K photos
37 videos
3 files
172 links
ይህ ትክክለኛ የኤፍ ኤም አዲስ 97.1 የቴሌግራም ቻናል ነው
Download Telegram
ኢቢሲ ከአዲሱ የጅማ ስቱዲዩ ልዩ የምርቃት ስነ-ስርአት በቀጥታ ስርጭት እያስተላለፈ ይገኛል
https://www.facebook.com/EBCzena/videos/427425130362005
ዛሬ የሚመረቀው የኢቢሲ የጅማ ስቱዲዮ በምስል፦
ጂማ ስቱዲዮ - ተጨማሪ የይዘት ምንጭ
#etv #EBC #Jimma
🔥5👍1
የፕሮግራም ጥቆማ ለሀገር ልጆች

ከቅኝት ስፖርት አዘጋጆች
አርሰናል ከ ፒኤስጂ

በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የ2024/25 የውድድር ዓመት የ2ኛ ሳምንት መርሐግብር በሰሜን ለንደን ኤምሬትስ ስቴዲየም ላይ ዛሬ ማክሰኞ ምሽት 4:00 የእንግሊዙ አርሰናል ከፈረንሳዩ ፓሪሰን ዠርሜ ጋር የሚያደርጉትን አጓጊ ጨዋታ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ በኤፍኤም አዲስ 97.1 ላይ ቅኝት ስፖርቶች ወደናንተ ያደርሳሉ።

ጨዋታውን በኤፍኤም አዲስ 97.1 ላይ በሬዲዮ፣ በሳተላይት ቴሌቪዥን፣በዩቲዩብና በፌስቡክ ገጾቻችን በፈለጉት አማራጭ መከታተል ይችላሉ!!

የጨዋታውን ትክክለኛ ግምት በማስቀመጥ የካርድ ሽልማቶችን ያግኙ!!

ፕሮግራሙን ቅኝት ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፕሬሽን ጋር በመተባበር በኤፍኤም አዲስ 97.1 ላይ ያቀርቡታል።

ሙሉ ጨዋታን ቀጣዩን ሊንክ በመጫን በዩቱዮብ ገፃችን ይከታተሉ::

@FMADDIS97.1-qw6tj
6👍3👎1🔥1😁1
የአባገዳ ባንዲራ ቀለማት እና የቀለማቱ አቀማመጥ ትርጉም
*********************

የአባገዳ ባንዲራ ቀለማት አቀማመጥ ከላይ ወደ ታች
ጥቁር፣
ቀይ፣
ነጭ ነው።
ጥቁር መደብ፦ የፈጣሪ የበላይ መሆንን የሚገልጽ ነው። የኦሮሞ ሕዝብ ራሱ ጥቁር እንደሆነው ሁሉ ፈጣሪው /ዋቃ/ ጥቁር ነው ብሎ ያምናል። ጥቁር ቀለምም በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ የቀዳሚነት መገለጫ ነው። ጥቁሩ ፈጣሪ ያለው ከላይ ነው፤ ዝናብ የሚዘንበው ከላይ ባለው ጥቁር ደመና ነው፣ ራሳችን ላይ ያለው ፀጉር እስኪሸብት ድረስ ጥቁር ነው፤ የዓይናችን ብሌን ጥቁር ነው - የሚገኘውም ከላይ ነው። እናም ጥቁር ቀዳሚ የመሆን መገለጫ ነው።

ቀይ መደብ፦ የብቃት፣ ብስል የመሆን፣ ሙሉ ሆኖ የመገኘት እና ለሕዝብ ነፃነት መሥዋዕት የመሆን መገለጫ ነው። ሁሉም ነገር በጊዜው ሙሉ ሆኖ የመገኘት ምሳሌ ነው። የኦሮሞ ሕዝብ አንድ ነገር የብቃት ደረጃው ላይ መድረሱን ሲገልጽ “diimate” /ቀላ/ ብሎ ይገልጻል።

ነጭ መደብ፦ የነገሮች ፍፃሜ መገለጫ ነው። እንደ ምሳሌ፦ ጠቁሮ ዝናብ የሚሰጠን ደመና ነጭ ሲሆን አይዘንብም ማለት ነው፤ ጥቁር የነበረው የሰው ፀጉር እርጅና ሲደርስ ይሸብታል (ነጭ ይሆናል)፣ ነዶ ያለቀ እንጨት አመዱ ነጭ ነው … ስለዚህ ነጭ የፍፃሜ መገለጫ ነው ብሎ ያምናል - የኦሮሞ ሕዝብ።
#ኢሬቻ #etv #EBC
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0253oMPjoupdgwMWm1VF6ajSAWXxxfihs7dUixTcNezadBhVKL3vm4YhggLecPRtipl
👍6👎1😁1
ፍቅር እና መተሳሰብ የሚነግስበት በዓል
📷 በአሰግድ አሰፋ
#etv #EBC #ኢሬቻ
ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላለፉ
***********
የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል ምክንያት በማድረግ ለመላው የኦሮሞ ህዝብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል።
"ለመላው የኦሮሞ ሕዝብ እንኳን ለ2017 ዓ.ም የኢሬቻ በዓል በሠላም እና በጤና አደረሳችሁ" ብለዋል ፕሬዚዳንቷ በመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክታቸው።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0wofp3nGDuK2PHAyvHSw4LxRvaJcX3tub4gDUNuntYjdQDXEVgKgr8usmqKMAq9rgl
በኢሬቻ በዓላት ላይ በስፋት የሚታየው "ጥቁር፣ ቀይ እና ነጭ" ቀለማት ያሉት ባንዲራ ትርጉም ምንድነው??
*********************

ከላይ ወደ ታች ጥቁር፣ ቀይ፣ ነጭ ቀለማት ያሉት የአባገዳ ባንዲራ

በተለይ በአዲስ አበባ እና በቢሾፍቱ በድምቀት በሚከበሩት የኦሮሞ ሕዝብ የኢሬቻ በዓላት ላይ በሚሳተፉ የበዓሉ ታዳሚዎች እጅ ላይ የማይጠፋው ባንዲራ አስገራሚ የቀለማቱ አደራደር እና ትርጓሜ የሚከተለውን ይመስላል፦

👉ጥቁር መደብ፦ ፈጣሪ የበላይ መሆኑን የሚገልጽ ነው። የኦሮሞ ሕዝብ ራሱ ጥቁር እንደሆነው ሁሉ ፈጣሪው /ዋቃ/ ጥቁር ነው ብሎ ያምናል። ጥቁር ቀለምም በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ የቀዳሚነት መገለጫ ነው። ጥቁሩ ፈጣሪ ያለው ከላይ ነው፤ ዝናብ የሚዘንበው ከላይ ባለው ጥቁር ደመና ነው፣ ራሳችን ላይ ያለው ፀጉር እስኪሸብት ድረስ ጥቁር ነው፤ የዓይናችን ብሌን ጥቁር ነው - የሚገኘውም ከላይ ነው። እናም ጥቁር ቀዳሚ የመሆን መገለጫ ነው።

👉ቀይ መደብ፦ የብቃት፣ ብስል የመሆን፣ ሙሉ ሆኖ የመገኘት እና ለሕዝብ ነፃነት መሥዋዕት የመሆን መገለጫ ነው። ሁሉም ነገር በጊዜው ሙሉ ሆኖ የመገኘት ምሳሌ ነው። የኦሮሞ ሕዝብ አንድ ነገር የብቃት ደረጃው ላይ መድረሱን ሲገልጽ “diimate” /ቀላ/ ብሎ ይገልጻል።

👉ነጭ መደብ፦ የነገሮች ፍፃሜ መገለጫ ነው። እንደ ምሳሌ፦ ጠቁሮ ዝናብ የሚሰጠን ደመና ነጭ ሲሆን አይዘንብም ማለት ነው፤ ጥቁር የነበረው የሰው ፀጉር እርጅና ሲደርስ ይሸብታል (ነጭ ይሆናል)፣ ነዶ ያለቀ እንጨት አመዱ ነጭ ነው … ስለዚህ ነጭ የፍፃሜ መገለጫ ነው ብሎ ያምናል - የኦሮሞ ሕዝብ።

#ኢሬቻ #etv #EBC
😁1
የሆረ ፊንፊኔ የኢሬቻ በዓል በድምቀት እየተከበረ ነው
**************
የ2017 ዓ.ም የሆረ ፊንፊኔ የኢሬቻ በዓል ባህላዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ በልዩ ልዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል።
የበዓሉ ሥነ-ሥርዓት በገዳ ሥርዓት መሰረት በአባ ገዳዎች ምርቃት የተጀመረ ሲሆን፤ ሌሊቱን ወደ ስፍራው ሲያቀኑ ያደሩት የበዓሉ ተሳታፊዎች በአሁኑ ሰዓት በዓሉን አድምቀውታል።
ከአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ ወደ ሆረ ፊንፊኔ የተመሙት የበዓሉ ታዳሚዎች በባህሉ መሰረት ለፈጣሪ ምስጋና በማቅረብ ላይም ሲሆኑ፤ በባህላዊ አልባሳት ያጌጡ ወጣቶችም በቡድን ቡድን እየሆኑ ባህላዊ ዜማዎችን በማዜም በዓሉን እያከበሩ ይገኛሉ።
📷 በሜሮን ንብረት ፣ በአሰግድ ሲሳይ እና በአፎሚያ ክበበው
#ኢሬቻ #etv #EBC
👍2