ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሐረር ከተማ ያስገነቡት የዳቦና ዱቄት ፋብሪካ ሥራ ጀመረ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሐረር ከተማ ያስገነቡትን 7ኛውን የዳቦና ዱቄት ፋብሪካ ከሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ ሚስራ አብደላ ጋር በመሆን ስራ አስጀምረዋል።
ፋብሪካው በቀን 300 ሺ ዳቦና 420 ኩንታል ዱቄት ያመርታል።
በሶስት ፈረቃ ከ150 በላይ ሰዎች የስራ እድል የሚፈጥር መሆኑንም የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
በቀጣይም በአምስት ከተሞች እየተገነቡ ያሉትን ፋብሪካወች ተጠናቀው ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ግንባታቸው እየተፋጠነ ይገኛልም ብሏል፤ ጽህፈት ቤቱ።
ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓ.ም
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሐረር ከተማ ያስገነቡትን 7ኛውን የዳቦና ዱቄት ፋብሪካ ከሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ ሚስራ አብደላ ጋር በመሆን ስራ አስጀምረዋል።
ፋብሪካው በቀን 300 ሺ ዳቦና 420 ኩንታል ዱቄት ያመርታል።
በሶስት ፈረቃ ከ150 በላይ ሰዎች የስራ እድል የሚፈጥር መሆኑንም የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
በቀጣይም በአምስት ከተሞች እየተገነቡ ያሉትን ፋብሪካወች ተጠናቀው ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ግንባታቸው እየተፋጠነ ይገኛልም ብሏል፤ ጽህፈት ቤቱ።
ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓ.ም
#ኢፕድ_ድንቃድንቅ‼️
ታምረኛው ቤተሰብ ‼️
ከወደ ፓኪስታን “ተዓምር ነው” የተባለ ዜና ተሰምቷል፡፡ ዜናው ፓኪስታናዊያንን ብቻ አስገርሞ አልቀረም።
ይልቁንም ጉዳዩ እንግዳ ነገር በመሆኑም ጭምር በዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ ላይም “አጃኢብ” ተበሎ ሰፍሯል።
ነገሩ እንዲህ ነው። ጥንዶቹ በፓኪስታን ላርካና ነዋሪ ናቸው፡፡ ባልና ሚስቱ አሚር አሊና ከዲጃ ይባላሉ፡፡ የሁለቱም የልደት ቀን ተመሳሳይ ነው፤ እአአ ኦገስት አንድ፡፡
ጥንዶቹ ይህን ልዩ ቀን ታሪካዊ ለማድረግ አሰቡ፡፡ መላም ዘየዱ፡፡
አደረጉትም። በልደት ቀናቸው በአንድ ጣሪያ ስር ለመኖር ወስነው በጎርጎሮሳዊያኑ የጊዜ ቀመር ኦገስት 1 ቀን 1991 በልደት ቀናቸው ተጋቡ።
በተጋቡ ልክ በአንድ አመታቸው ቤታቸው በልጅ ተባረከ። በባልና ሚስቱ የልደት ቀንና የጋብቻ ቀን መመሳሰል የተጀመረው ግጥምጥሞሽ ወደ በኩር ልጃቸውም ተሻገረ።
ጥንዶቹ የመጀመሪያ ልጃቸውን በልደት ቀናቸው ወለዱ። ስሟንም ሲንዶ አሏት።
የጥንዶቹ ተዓምር የሚመስል ህይወት በዚህ አላበቃም፡፡
የአምላክ ድንቅ ስራ በዚህ ቤተሰብ ቀጥሎ፤ ጥንዶቹ ሁለት መንታ ሴት ልጆችን አሁንም በተመሳሳይ የልደት ቀናቸውን በሚያከብሩበት ኦገስት 1 ወለዱ። ተገረሙ፤ ብዙዎችንም አስደመሙ።
የቤተሰቡ ታምራት እንደቀጠለ ነው።
ባልና ሚስቱ ሌለ መንታ ወንድ ልጆችን አቅፈው ሳሙ። እነዚህ መንታ ወንድማማቾችም ይህችን ምድር የተቀላቀሉት እህቶቻቸው በተወለዱበት ወላጆቻቸው ደግሞ በተወለዱበትና በተጋቡበት ቀን መሆኑ ግርምቱን ከፍ አደረገው።
ጥንዶቹ በአምላክ ስራ እየተገረሙም እየተደነቁም የራሳቸውንና የአምስቱን ልጆቻቸውን ልደት በተመሳሳይ ቀን እያከበሩ ኑሯቸውን መግፋት ቀጠሉ።
የቤተሰቡ ታምር በዚህ እንዲቋጭ አልተፈለገምና ጥንዶቹ ዳግም ሁለት ሴት ልጆችን አከታትለው ወለዱ።
የሚገርመው ታዲያ ሁለቱም በተለያየ አመት ይወለዱ እንጂ የተወለዱበት ቀን ግን እንደ ቤተሰቡ ሁሉ ተመሳሳይ ነበር፤ ኦገስት 1።
ስለዚህ ጉዳይ ሲጠየቅ አባት አሚር አሊ ስለመደነቁና መደሰቱ ይናገራል፡፡
ባለቤቱ ከዲጃም ሁልጊዜ ድንቅና ስኬታማ ስለሆነው የወሊድ ታሪክ እንደምትደነቅ ተናግራለች። ባልና ሚስቱ ይሄን ጉዳይ ከፈጣሪ የተሰጠ ድንቅ ስጦታ አድርገው ተቀብለውታል፡፡
የአለም ድንቃድንቅ መዝገብም ገዳዩን ሰምቶ ብቻ ማለፍአልፈለገም። በዚህ ጉዳይ ላይ ከዚህ ቀደም የተመዘገበ ነገር እንዳለ መለስ ብሎ አጣራ።
ከእነዚህ ቤተሰቦች ቀድሞ አሜሪካውያን የአምስት ቤተሰብ አባላት ተመሳሳይ የልደት ቀን ኖሯቸው መዝገቡ ላይ ሰፍረው ተገኙ። ሆኖም ፓኪስታናዊያኑ ዘጠኝ በመሆናቸው በድንቃድንቅ መዝገቡ ላይ ከመስፈር ያገዳቸው አልነበረም።
አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ
https://www.tiktok.com/@ethiopianpressagency...
ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓም
በዳግማዊት ግርማ
ታምረኛው ቤተሰብ ‼️
ከወደ ፓኪስታን “ተዓምር ነው” የተባለ ዜና ተሰምቷል፡፡ ዜናው ፓኪስታናዊያንን ብቻ አስገርሞ አልቀረም።
ይልቁንም ጉዳዩ እንግዳ ነገር በመሆኑም ጭምር በዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ ላይም “አጃኢብ” ተበሎ ሰፍሯል።
ነገሩ እንዲህ ነው። ጥንዶቹ በፓኪስታን ላርካና ነዋሪ ናቸው፡፡ ባልና ሚስቱ አሚር አሊና ከዲጃ ይባላሉ፡፡ የሁለቱም የልደት ቀን ተመሳሳይ ነው፤ እአአ ኦገስት አንድ፡፡
ጥንዶቹ ይህን ልዩ ቀን ታሪካዊ ለማድረግ አሰቡ፡፡ መላም ዘየዱ፡፡
አደረጉትም። በልደት ቀናቸው በአንድ ጣሪያ ስር ለመኖር ወስነው በጎርጎሮሳዊያኑ የጊዜ ቀመር ኦገስት 1 ቀን 1991 በልደት ቀናቸው ተጋቡ።
በተጋቡ ልክ በአንድ አመታቸው ቤታቸው በልጅ ተባረከ። በባልና ሚስቱ የልደት ቀንና የጋብቻ ቀን መመሳሰል የተጀመረው ግጥምጥሞሽ ወደ በኩር ልጃቸውም ተሻገረ።
ጥንዶቹ የመጀመሪያ ልጃቸውን በልደት ቀናቸው ወለዱ። ስሟንም ሲንዶ አሏት።
የጥንዶቹ ተዓምር የሚመስል ህይወት በዚህ አላበቃም፡፡
የአምላክ ድንቅ ስራ በዚህ ቤተሰብ ቀጥሎ፤ ጥንዶቹ ሁለት መንታ ሴት ልጆችን አሁንም በተመሳሳይ የልደት ቀናቸውን በሚያከብሩበት ኦገስት 1 ወለዱ። ተገረሙ፤ ብዙዎችንም አስደመሙ።
የቤተሰቡ ታምራት እንደቀጠለ ነው።
ባልና ሚስቱ ሌለ መንታ ወንድ ልጆችን አቅፈው ሳሙ። እነዚህ መንታ ወንድማማቾችም ይህችን ምድር የተቀላቀሉት እህቶቻቸው በተወለዱበት ወላጆቻቸው ደግሞ በተወለዱበትና በተጋቡበት ቀን መሆኑ ግርምቱን ከፍ አደረገው።
ጥንዶቹ በአምላክ ስራ እየተገረሙም እየተደነቁም የራሳቸውንና የአምስቱን ልጆቻቸውን ልደት በተመሳሳይ ቀን እያከበሩ ኑሯቸውን መግፋት ቀጠሉ።
የቤተሰቡ ታምር በዚህ እንዲቋጭ አልተፈለገምና ጥንዶቹ ዳግም ሁለት ሴት ልጆችን አከታትለው ወለዱ።
የሚገርመው ታዲያ ሁለቱም በተለያየ አመት ይወለዱ እንጂ የተወለዱበት ቀን ግን እንደ ቤተሰቡ ሁሉ ተመሳሳይ ነበር፤ ኦገስት 1።
ስለዚህ ጉዳይ ሲጠየቅ አባት አሚር አሊ ስለመደነቁና መደሰቱ ይናገራል፡፡
ባለቤቱ ከዲጃም ሁልጊዜ ድንቅና ስኬታማ ስለሆነው የወሊድ ታሪክ እንደምትደነቅ ተናግራለች። ባልና ሚስቱ ይሄን ጉዳይ ከፈጣሪ የተሰጠ ድንቅ ስጦታ አድርገው ተቀብለውታል፡፡
የአለም ድንቃድንቅ መዝገብም ገዳዩን ሰምቶ ብቻ ማለፍአልፈለገም። በዚህ ጉዳይ ላይ ከዚህ ቀደም የተመዘገበ ነገር እንዳለ መለስ ብሎ አጣራ።
ከእነዚህ ቤተሰቦች ቀድሞ አሜሪካውያን የአምስት ቤተሰብ አባላት ተመሳሳይ የልደት ቀን ኖሯቸው መዝገቡ ላይ ሰፍረው ተገኙ። ሆኖም ፓኪስታናዊያኑ ዘጠኝ በመሆናቸው በድንቃድንቅ መዝገቡ ላይ ከመስፈር ያገዳቸው አልነበረም።
አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ
https://www.tiktok.com/@ethiopianpressagency...
ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓም
በዳግማዊት ግርማ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ ረፋድ ላይ በካይሮ በተካሄደው ‘የሱዳን ጎረቤት ሀገሮች ጉባዔ’ ላይ ተሳትፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው በግብፅ የተካሄደውን የመሪዎች ጉባኤን ጨምሮ ሱዳን ለተፈጠረው ቀውስ እፎይታ ለማምጣት የተጀመሩ የተለያዩ ጥረቶችን እውቅና ሰተው በሱዳን ያለውን ግጭት ለመፍታት በኢጋድ መሪነት እና ከአፍሪካ ህብረት ድጋፍ ሰጪነት የተጀመረውን ነባር ውይይቶች ጋር ማጣጣም እንደሚያስፈልግ መግለፃቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካቸው የግብፅ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል።
ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓ. ም
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው በግብፅ የተካሄደውን የመሪዎች ጉባኤን ጨምሮ ሱዳን ለተፈጠረው ቀውስ እፎይታ ለማምጣት የተጀመሩ የተለያዩ ጥረቶችን እውቅና ሰተው በሱዳን ያለውን ግጭት ለመፍታት በኢጋድ መሪነት እና ከአፍሪካ ህብረት ድጋፍ ሰጪነት የተጀመረውን ነባር ውይይቶች ጋር ማጣጣም እንደሚያስፈልግ መግለፃቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካቸው የግብፅ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል።
ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓ. ም
የኢትዮጵያ እና የግብጽ ግንኙነት ላይ በጋራ የተሰጠ መግለጫ‼️
ዛሬ ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓ.ም የአረብ ሪፐብሊክ ግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ተቀብለው አነጋግረዋል።
መሪዎቹ ባደረጉት ምክክር የሁለቱን ሃገራት ህዝቦች የጋራ ጥቅም ባስጠበቀና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ በግብፅና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህልና የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማሻሻል ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
የመሪዎቹ ቁርጠኝነት በቀጠናው ሰላምና ደህንነትን ለማስፈንና መረጋጋትን ለማስጠበቅ ከሚያበረክተው አስተዋፅኦ ባሻገር ሃገራቱ የሚያጋጥሟቸውን የጋራ ፈተናዎች ለመሻገርም ያስችላል።
ሁለቱ መሪዎች ባደረጉት ምክክር የታላቁ የህዳሴ ግድብ ድርድርን በተመለከተ በተከታዮቹ ሁለት ነጥቦች ላይ ተስማምተዋል፤
👉 የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌትንና የአሰራር ደንቦችን በተመለከተ በግብፅ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል የሚካሄደውን ንግግር በፍጥነት ለማስጀመር እንዲሁም ንግግሩን በአራት ወራት ውስጥ አጠናቆ ከመግባባት ላይ ለመድረስ አስፈላጊውን ሁሉ ጥረት እንደሚያደርጉ ተስማምተዋል።
👉 ንግግሩ በሚካሄድበት ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ በ2015-2016 ዓ.ም የግድቡ የውሃ ሙሌት ወቅት ግብፅና ሱዳን ከወንዙ በሚያገኙት የውሃ አቅርቦት ላይ የጎላ ችግር እንዳያጋጥም ለማድረግ ኢትዮጵያ ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጣለች።
ዛሬ ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓ.ም የአረብ ሪፐብሊክ ግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ተቀብለው አነጋግረዋል።
መሪዎቹ ባደረጉት ምክክር የሁለቱን ሃገራት ህዝቦች የጋራ ጥቅም ባስጠበቀና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ በግብፅና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህልና የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማሻሻል ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
የመሪዎቹ ቁርጠኝነት በቀጠናው ሰላምና ደህንነትን ለማስፈንና መረጋጋትን ለማስጠበቅ ከሚያበረክተው አስተዋፅኦ ባሻገር ሃገራቱ የሚያጋጥሟቸውን የጋራ ፈተናዎች ለመሻገርም ያስችላል።
ሁለቱ መሪዎች ባደረጉት ምክክር የታላቁ የህዳሴ ግድብ ድርድርን በተመለከተ በተከታዮቹ ሁለት ነጥቦች ላይ ተስማምተዋል፤
👉 የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌትንና የአሰራር ደንቦችን በተመለከተ በግብፅ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል የሚካሄደውን ንግግር በፍጥነት ለማስጀመር እንዲሁም ንግግሩን በአራት ወራት ውስጥ አጠናቆ ከመግባባት ላይ ለመድረስ አስፈላጊውን ሁሉ ጥረት እንደሚያደርጉ ተስማምተዋል።
👉 ንግግሩ በሚካሄድበት ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ በ2015-2016 ዓ.ም የግድቡ የውሃ ሙሌት ወቅት ግብፅና ሱዳን ከወንዙ በሚያገኙት የውሃ አቅርቦት ላይ የጎላ ችግር እንዳያጋጥም ለማድረግ ኢትዮጵያ ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጣለች።