Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
1445ኛው የኢድል አል አድሃ (አረፋ) በዓል በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነስርዓት እየተከበረ ይገኛል‼️
አውሮፕላኖቹ ከኢትዮጵያ አልፎ ለጎረቤት ሀገራት አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ናቸው
*****
(ኢ ፕ ድ)
የአሰሳና የርጭት አውሮፕላኖቹ ከኢትዮጵያ አልፎ ለጎረቤት ሀገራት አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ግብርናውን ለማዘመንና ምርትን ለማሳደግ በትኩረት እየሠራች ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የስንዴና ሌሎች ሰብሎች ላይ በአንበጣ፣በግሪሳ ወፍና በተምች እየተጠቃች ትገኛለች። እነዚህን ተባዮች ሙሉ ለሙሉ ማስቀረት የማይቻል ቢሆንም የመቀነስና ለመከላከል የሚያስችል አቅም መፍጠር አስፈላጊ ነዉ።

የርጭትና የአሰሳ አውሮፕላኖችን እየተከራዩ ለመከላከል ከመሞከር ይልቅ የራስ አቅም ማደራጀት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ በ850 ሚሊዮን ብር ወጪ አምስት አውሮፕላኖች.......

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130019
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
የአንዋር መስጊድ ኢማም ሀጅ ጦሃ ሃሩን ስለኢድ አልአድሃ በዓል ይናገራሉ‼️

👉 ሀጅ ማድረግ ከአምስቱ የእስልምና መሠረቶች አንዱ ነው። ሰዎች በሕይወት ዘመናቸው ቢያንስ አንድ ጊዜ መካን ዘይረው መመለስ አለባቸው። መካ በመገኘትም የተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችን ያከናውናሉ

👉 የዒድ አል-አድሃ ታሪካዊ ዳራ ነቢዩ ኢብራሂም ልጃቸውን ለአላህ ለመሰዋት ያደረጉት ቁርጠኝነት የተመላበት ውሳኔ እና ለመስዋዕትነት የቀረበው ልጅ ያሳየው የተለየ ጽናት ነው፣

👉 ሁለቱ ሰዎች ለፈጣሪ መታዘዝን በግልጽ ያሳዩባት ያቺ ዕለት የዒድ አል-አድሃ በዓል ሆና እንድትከበር ተወሰነ፣

👉 የኢድ አልአድሃ በዓል በሁለት አይነት መልኩ ይከበራል። አንደኛው ኃይማኖታዊ መስፈርቶችን ጠብቆ ወደ መካ በመሄድ የሚደረግ የጸሎት ሥነሥርዓት ነው፣

👉 ሁለተኛው ወደ መካ ለመሄድ ዕድልን ያላገኙ በሀገር ውስጥ የኢድ አልአድሃን በዓል ያከብራሉ። ከሰላት በኋላ አቅም ያላቸው ሰዎች በግና ሌሎች እንስሳትን በማረድ አቅም ለሌላቸው በማካፈል በዓሉን በጋራ ያሳልፋሉ።

👉 በአረፋ መረዳዳትና መደጋገፍ ቢስተዋልም በዚህ ወቅት ሚስተዋለው መደጋገፍ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በየጊዜው የሚከናወን ተግባር ሊሆን ይገባል፣

👉 የደካሞችን ቤት በማደስ፣ የዕለት ጉርሳቸውን ማቅረብ ፤የታረዙትን ማልበስ በኢድ አልአድሃ የሚወደድ ተግባር ቢሆንም በሌሎችም ቀናት እነዚህ በጎ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ የሚገባቸው ናቸው፣

👉 ማኅበረሰቡ በበዓል ወቅት ከመረዳዳት ባሻገር ሀገራዊ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ በጋራ መቆምም ይጠበቅበታል፣

👉 ሰዎች በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ምክንያቶች ጉዳት ሲደርስባቸው፤ ከአካባቢያቸው ሲፈናቀሉ፤ ሲራቡና ሲጠሙ ዝም ብሎ መመልከት ከእስልምና አስተምሮ አንጻር የሚያስጠይቅ ነው፣

https://press.et/?p=129953
በ850 ሚሊዮን ብር የተገዙ አምስት ዘመናዊ የኬሚካል ርጭትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጡ ዘመናዊ የርጭት አውሮፕላኖች (ኤር ትራክተርስ)‼️
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
የነቀምቴ ጉዲና ቱምሳ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የበረራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሄደ
********************
(ኢ ፕ ድ)

የነቀምቴ ጉዲና ቱምሳ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የበረራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሰታወቁት የአውሮፕላን ማረፊያው ተገንብቶ አገልግሎት መጀመር በአካባቢው የሚገኘውን የተፈጥሮ ጸጋ በተሻለ ለማልማት እና የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማስፋት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል፡፡

አካባቢው ያለውን የቱሪዝም ሀብት ጥቅም ላይ ለማዋል፣ የሕዝቦችን ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ለማቀላጠፍ ብሎም በአጠቃላይ የሕዝቡን ሕይወት ለመቀየር ጉልህ ሚና አለው ብለዋል፡፡

በበረራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር አወሉ አብዲ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

በምሥራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ የተገነባ የሚገኘው የነቀምቴ ጉዲና ቱምሳ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የረጅም ዓመታት ጥያቄያቸውን የመለሰ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች መናገራቸውን ከኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የማኀበራዊ የትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓም